“ቅዱስ ገብርኤል ሆይ አውጣኝ አልኩት ጸሎቴን ሰምቶ አወጣኝ”……”የቀድሞው የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ ምስክርነት !!!
የሐዋሳ ከተማ የቀድሞ ከንቲባ ረዳት ፕሮፌሰር ጸጋዬ ቱኬ በሐሰት በተከሰሱበት የክስ መዝገብ 13 ዓመት ተፈርዶባቸው ወደ ወህኒ ሲወረወሩ በእስር ቤት ሆነው ለቅዱስ ገብርኤል ጸሎት ልመናንን አቀረቡ።
“በአዉደ ምህረትህ ቆሜ ስለክብርህ መስከርያለሁና ለቂርቆስና እየሉጣ የደረስክ ቅዱስ ገብርኤል ሆይ አንተ ድረስልኝ ! የኔ እዉነት ተቀብሮ እንዳይቀር እርዳኝ” ሲል ተለማመኑት።
እነሆ መላእከ ብስራት ቅዱስ ገብርኤል በግፍ እና በበደል ለተገፉት ፈጥኖ መድረስ ባህሪው ነው እና ሰኔ 12 የዓመቱ ሚካኤል ቀን የባህራንን የሞት ደብዳቤ የሻረ አምላክ ከተፈረደባቸው የ 13 ዓመት የሐሰት እስራት ፍርድ በይግባኝ ነጻ ተብለው በሠላም ከቤተሰቦቻቸው ጋር ተቀላቀሉ።
እነሆ ድንቅ ታምር ያደረገላቸው እና ጸሎት ልመናቸውን የሰማውን ቅዱስ ገብርኤል በአውደ ምህረት ቆመው ትላንት አመስግነዋል። ስለታቸውንም 5000 ብር አስገብተዋል።
