የሁቲዎች አዲስ ትዕዛዝ

Date:

የየመን ሁቲዎች ከእስራኤል ወደቦች ጋር ስምምነት ያለው የትኛውም መርከብ እንደሚመታ አስጠነቀቁ።

”የየትኛውም ኩባንያ መርከብ በየትኛውም አገር ሰንደቅ ዓላማ ስም ይንቀሳቀስ ዒላማ ይሆናል” በሚል ዝተዋል።

ሁቲዎች ወደ 4ኛው ምዕራፍ  የእስራኤል የባህር እንቅስቃሴን  መዝጋት እርምጃ እንደሚገቡ በወታደራዊ ቃል አቀባያቸው ያህያ ሳሬ በኩል ይፋ አድርገዋል።

የሁቲ ሀይል የጦር መሳሪያ መድረስ በሚችልበት ቦታ ሁሉ መርከቦቹ ይመታሉ ነው ጥቅል ሀሳቡ።

እሁድ አመሻሹን መግለጫ የሰጠው ሁቲ አሁንም ለፍልስጤማውያን ያለውን አጋርነት አጠናክሮ እንደሚገፋበት ግልጽ አድርጓል።

ከቴል አቪቭ ጋር ስምምነት ያለው መርከብ ሁሉ ዒላማ እንደሚደረግ አንስራላሆች አረጋግጠዋል።

በተጨማሪም በቀይ ባህር እና ህንድ ውቅያኖስ በኩል በተለይም በበብ-ኤል መንደብ ሰርጥ መርከቦች እንዳይንቀሳቀሱ አድርገው መሰንበታቸውም አይዘነጋም።

በዓመት ከ1  ትሪሊዬን ዶላር በላይ ምርት ይተላለፍበታል በሚባለው ቀጠና ላይ ከባድ ጫና ሲያሳድሩም ቆይተዋል።

የመርከቦችን ጉዞም በኬፕ ኦፍ ጉድ ሆፕ ደቡባዊ አፍሪካ ጫፍ እንዲሆን በማስገደድ የቀይ ባህርን የንግድ ታሪክ 155 ዓመታት ወደ ኋላ መልሰውታል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከባድ ሙስና የተከሰሱትን 4 ተከሳሾችን፤ ፖሊስ ፍርድ ቤት ማቅረብ ሳይችል ቀረ

በከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመስርቶባቸው በፖሊስ የ'ይፈለጋሉ" ማስታወቂያ የወጣባቸው...

ስለመካከለኛው ምስራቅ አዲስ ውጥረት እስካሁን የታወቁ ጉዳዮች

🔸 ትላንት ምሽት ከኢራን ግዛት የተተኮሰ የሮኬት ጥቃት በሰሜናዊ...

የወንጀል ሥነ-ሥርዓትና ማስረጃ ሕጉ በጋዜጣ እስኪታተም ረቂቅ ሰነዶችን ከመጠቀም እንዲቆጠብ የፍትሕ ሚኒስቴር አሳሰበ

የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. የፍትሕ ሚኒስቴር አዲሱ የወንጀል ሕግ ሥነ-ሥርዓትና ማስረጃ ሕግ...

ፔንታጎን የእስራኤል ስለላ እንደሚያሳስበው ተገለጸ

ከቅርብ ሳምንታት ወዲህ ፔንታጎን እስራኤል ከፍተኛ ልዑኮችን ጨምሮ የአሜሪካ...