የህብረት ስራ ማህበራት ባክኖ የነበረ 1.6 ቢሊየን ብር ማስመለስ ተችሏል አሉ

Date:

ሌሎችም በርካታ ውጤቶች በኀብረት ሥራ ማህበራት የሪፎርም ስራ መመዝገባቸውን የኢትዮጵያ ኅብረት ሥራ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር አቶ ሺሰማ ገብረሥላሴ ተናግረዋል።

ለአብነትም ማህበቱን በማዋሀድ፣ በማፍረስና ማጠናከር በተሰራው ስራ ከ120 ሺህ በላይ  የነበረው የኀብረት ሥራ ማህበራት ቁጥር አሁን ላይ ወደ 89 ሺህ ዝቅ ማለቱን ጠቅሰዋል።

የአመራር ስርአታቸውን ለማሻሻል በተሰራው ስራም ከ6900 መሰረታዊ ማህበራትና 57 ዩኒየኖች የአመራር ለውጥ አድርገዋል ያሉት አቶ ሺሰማ ወደ 4300 የሚሆኑ ሴቶችና ወጣቶች በአመራርነት እንዲካተቱ መደረጉንም ተናግረዋል።

አዳዲስ አባላትን በማፍራት የኀብረት ሥራ ማህበራት ዓመታዊ ካፒታል የማፍራት አፈፃፀማቸውን እንዲያሳድጉ እና  የቁጠባ መጠን እንዲጨምሩ ማድረግ መቻሉንም አመልክተዋል::

በከተሞች የምርት አቅርቦትና ግብይት ላይ በተሰራው ስራም በሀገር አቀፍ ደረጃ 378 ኀብረት ስራ ማህበራት ከ1400 በላይ በሚሆኑ የቅዳሜ እና እሁድ ገበያዎች ተሳትፈው ዋጋ እያረጋገጡ ይገኛሉ ብለዋል።

12ኛው የኅብረት ሥራ ማህበራት ኤግዚቢሽን፣ ባዛርና ሲምፖዚየም ከጥር 26 እስከ 30 ቀን 2018  በአዲስ አበባ ኤግዚቢሽን ማዕከልና በአድዋ ድል መታሰቢያ እንደሚካሄድ ተነግሯል።

“ኅብረት ሥራ ከምርት እስከ ግብይት፤ ከአምራች እስከ ሸማች” በሚል መሪ ሃሳብ በሚዘጋጀው ኤግዚቢሽን እና ባዛር ላይ 360 የሚሆኑ የኅብረት ሥራ ማህበራት ይሳተፋሉ ተብሏል።

ማህበረሰቡ ለዕለት ተዕለት ፍጆታው የሚጠቀምባቸው ከ22 ሺህ ኩንታል በላይ ምርቶች በተመጣጣኝ ዋጋ ይቀርቡበታል የተባለ ሲሆን ፤ ከ300 ሚሊዮን ብር በላይ ቀጥታ ግብይት ይፈጸማል ተብሎ እንደሚጠበቅም ኮሚሽኑ የላከን መረጃ ያመለክታል።

ንጋቱ ረጋሳ (ሸገር 102.1)

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የጣሊያን ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ ሜሎኒ አዲስ አበባ ገቡ

ጠቅላይ ሚኒስትሯ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ ጠቅላይ...

የቴሌኮም ኦፕሬተሮች የ5 በመቶ የአደጋ ሥጋት ምላሽ ፈንድ ክፍያን ተግባራዊ ማድረግ ጀመሩ

በኢትዮጵያ የሚንቀሳቀሱት ሁለቱም የቴሌኮም ኦፕሬተሮች ማለትም ኢትዮ ቴሌኮም እና...

የአውሮፓ ፓርላማ ፕሬዚዳንት ለኢራን ህዝብ – “እኛ ከእናንተ ጋር ነን”

የአውሮፓ ፓርላማ ፕሬዝዳንት ሮቤርታ ሜትሶላ፥ የኢራን መንግስት በተቃዋሚዎች ላይ...

አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ ውክልና ሊኖራት ይገባል

በተባበሩት መንግስታት የፀጥታው ምክር ቤት አፍሪካ ቋሚ ውክልና...