የረመዳን ወር ድሆችን፣ ችግረኞችንና ስደተኞችን በመደገፍ ማሳለፍ ይገባል

Date:

የረመዳን ወርን ከድሆች፣ ችግረኞች እና ስደተኞች ጋር በጋራ በመብላት፣ በመጠጣትና በመደገፍ ማሳለፍ ይገባል ሲሉሉ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ሼኽ ሐጅ ኢብራሂም ቱፋ አስገነዘቡ።

6ኛው ሀገራዊ የጎዳና ላይ ኢፍጣር መርሐ ግብር በአዲስ አበባ ከተማ መስቀል አደባባይ ተካሂዷል።

ሼኽ ሐጅ ኢብራሂም ቱፋ በመርሐ ግብሩ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት አንድነትን በተግባር የሚያሳየው የጎዳና ላይ ኢፍጣር መርሐ ግብር አስደሳች መሆኑን ገልጸው÷ የረመዳን ወር የቸርነት ወር በመሆኑ ከድሆች፣ ችግረኞችና ስደተኞች ጋር በጋራ ማሳለፍ ይገባል ብለዋል።

የእምነቱ ተከታዮች ለሀገራችን፣ ለወገናችን፣ ለአፍሪካ እና ለዓለም ሰላም ዱዓ ማድረግ ይገባል ብዋል።

በመርሐ ግብሩ ከፍተኛ የመንግሥት ስራ ኃላፊዎች፣ አምባሳደሮች፣ ዲፕሎማቶችና የሐይማኖቱ ተከታዮች ተገኝተዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በጤና አገልግሎት ማስታወቂያዎች ላይ የሕመምተኞችን ምስክርነት መጠቀም ተከለከለ

የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ባወጣው አዲስ መመሪያ መሠረት በኢትዮጵያ ውስጥ...

ሴቶችን በቤት ውስጥ በማገዝ  መልካም ማህበረሰብ መፍጠር ተጀምሯል

በቤት ውስጥ የሚሠሩ ተግባራትን ተከፋፍሎ በመሥራት ሴቶችና እናቶችን መደገፍ...

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ

የእግዚአብሔር ሕዝብ ጉባኤ፣ የጌታችንና የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አካልና የመንፈስ...

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ ቅርሶች ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰዋል

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ የአጼ ቴዎድሮስ የፀጉር ቁንዳል እና...