የሩሲያ ሙዚየም አፍሪካ ላይ ትኩረቱን ያደረገ ኤግዚቢሽን ሊያዘጋጅ ነው

Date:

የሞስኮው ፑሽኪን ስቴት የሥነ ጥበባት ሙዚየም ዳይሬክተር ኦልጋ ጋላክቲኖቫ አፍሪካ “ፍላጎት እና ሰኬትን መሳቧን የቀጠለች ትልቅ የባህል አድማስ
ነች” ብለዋል።

የአፍሪካ ባህል በሩሲያ ውስጥ ከፍተኛ ቦታ የሚሰጠው ቢሆንም አሁንም ብዙ የማይታወቁ ገጽታዎች እንዳሉት ጋላክቲዮኖቫ ለሩሲያ ሚዲያ ተናግረዋል።

በተለይም ብዙም የማይታወቀው የዘመናዊ አፍሪካ ጥበብ ሊታይ እንደሚገባው አጽንኦት ሰጥተዋል።

የሙዚየሙ ዳይሬክተር አክለውም በዚህ ጉዳይ ዙሪያ የተሠሩ ፕሮጀክቶች እንደሌሉ የገለፁ ሲሆን ሆኖም አሁን ላይ ለውጦች እንዳሉ ጠቁመዋል።

እ.አ.አ በ1912 የተመሠረተው እና ወደ 700 ሺህ የሚጠጉ ሥራዎችን የያዘው የፑሽኪን ሙዚየም በየዓመቱ እስከ 1.3 ሚሊዮን ጎብኚዎችን በመሳብ በሩሲያ በብዛት ከሚጎበኙ ሙዚየሞች አንዱ ነው።

@sputnik_ethiopia

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አባቴ ለእኔ አባት ብቻ አልነበረም፤ ለእናቴ ታማኝ ባል፣ ለሁላችንም ደግሞ የደስታ ምንጭ ነበር

"አባዬ… ዛሬ ላለሁበት ማንነት መሰረት የሆንከኝ አንተ ነህ!" ​የአርቲስት...

የአንበሶቹ ትንሳኤ፦ የዳካር እንባ እና የቴራንጋ ድል

​በዳካር ሰማይ ስር ዛሬ ጨረቃ አልወጣችም፤ ይልቁንም በሚሊዮን የሚቆጠሩ...

የጥምቀት በዓል በመላ ሀገሪቱ በድምቀት እየተከበረ ነው

የጥምቀት በዓል በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን እና በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት...

“ሎዛ ዘፀአት”እና “የሎዛ ድርሳናት”ተከታታይ ረጅም ልቦለድ መጻሕፍት ተመረቁ

በጋዜጠኛና ደራሲ መርዕድ እስጢፋኖስ የተጻፉት ሎዛ ዘፀአት(2014 ዓ.ም) እና...