የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የስድስተኛ ዙር ሰልጣኝ ዲፕሎማቶች ስልጠናን በኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ አስጀምሯል።
በማስጀመሪያ መርኃ ግብሩ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ (ዶ/ር)፣ በጠቅላይ ሚኒስትር ፅህፈት ቤት የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማዕከል አስተባባሪ ሚኒስትር ቢቂላ ሁሪሳ(ዶ/ር)፣ የውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ ጃፋር በድሩ፣ የሲቪል ሰርቪስ ዩንቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ንጉስ ታደሰ(ዶ/ር) እና ሰልጣኝ ዲፕሎማቶች ተገኝተዋል።
ስልጠናው ለቀጣይ 4 ወራት በሲቪል ሰርቪስ ዩንቨርሲቲ እንደሚሰጥም ተገልጿል።
ሰልጣኞች በቆይታቸው የፖሊሲ፣ የአካዳሚክ እና ተግባር ተኮር ስልጠናዎች እንደሚወስዱ ተመላክቷል።
ስልጠናው ከዚህ ቀደም ለአምስት ዙሮች የተሰጠ ሲሆን በስድስተኛው ዙር 50 ሰልጣኞች እንደሚሰለጥኑ ተመላክቷል።
