የስድስተኛ ዙር ሰልጣኝ ዲፕሎማቶች ስልጠና ጀመሩ

Date:

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የስድስተኛ ዙር ሰልጣኝ ዲፕሎማቶች ስልጠናን በኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ አስጀምሯል።

በማስጀመሪያ መርኃ ግብሩ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ (ዶ/ር)፣ በጠቅላይ ሚኒስትር ፅህፈት ቤት የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማዕከል አስተባባሪ ሚኒስትር ቢቂላ ሁሪሳ(ዶ/ር)፣ የውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ ጃፋር በድሩ፣ የሲቪል ሰርቪስ ዩንቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ንጉስ ታደሰ(ዶ/ር) እና ሰልጣኝ ዲፕሎማቶች ተገኝተዋል።

ስልጠናው ለቀጣይ 4 ወራት በሲቪል ሰርቪስ ዩንቨርሲቲ እንደሚሰጥም ተገልጿል።

ሰልጣኞች በቆይታቸው የፖሊሲ፣ የአካዳሚክ እና ተግባር ተኮር ስልጠናዎች እንደሚወስዱ ተመላክቷል።

ስልጠናው ከዚህ ቀደም ለአምስት ዙሮች የተሰጠ ሲሆን በስድስተኛው ዙር 50 ሰልጣኞች እንደሚሰለጥኑ ተመላክቷል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምርጫ በሚያካሂድባቸው ቦታዎች ሁሉ እሳተፋለሁ

በዘንድሮው ሀገራዊ ምርጫ እንደሚሳተፍ ያስታወቀው የኢትዮጵያ ዜጎች ለማሕበራዊ ፍትህ...

በሲዳማ ክልል ከ62% በመቶ በላይ የሚታረሰው መሬት በአሲዳማነት የተጎዳ ነዉ

በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ የሚታየው የምርታማነት ማነቆ በዋናነት የመሬት አሲዳማነት...

የኢትዮጵያ እዳ እና ሃብት አስተዳደር ኮርፖሬሽን የሥራ ኃላፊዎች ስብሰባ ሳይገኙ ቀሩ

የመንግስት ልማት ድርጅቶች ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የኢትዮጵያ እዳ እና...

የኢትዮጵያ እና ሕንድ የቆየ ዲፕሎማሲዊ ግንኙነት

የኢትዮጵያ እና ሕንድ የቆየ ዲፕሎማሲዊ ግንኙነት የአፍሪካ-ሕንድ...