የኢትዮጲያ ብሔራዊ ቡድን የፊታችን ሐምሌ 26 ወደ ሀገረ አሜሪካ አቅንቶ ከዲሲ ዩናይትድ ጋር የወዳጅነት ጨዋታዉን ለማድረግ ለ23 ተጫዋቾች ጥሪ በማድረግ ዝግጅት እያደረገ ይገኛል።
ብስራት ቴሌቪዥን ስፖርት ዝግጅት ከስፍራዉ አሁን በደረሰዉ መረጃ በርከት ያሉ የብሔራዊ ቡድኑ ተጨዋቾች ቪዛ መከልከላቸዉን ለማወቅ ተችሏል።
ቪዛ ከተከለከሉ የብሔራዊ ቡድኑ ተጫዋቾች መካከል ቢኒያም አይተን ፣ቢኒያም ገነቱ ፣መሀመድ አበራ ፣ወገኔ ገዛኸኝ፣በረከት ደስታ ፣ያሬድ ካሳዬ ናቸዉ።
ሌሎች የብሔራዊ ቡድኑ ተጫዋቾችም ተመሳሳይ ነገር ይገጥማቸዋል ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን የሌሎች ተጫዋቾችን ጉዳይ መረጃዉን እንዳገኘን ተመልሰን ይዘን የምንመጣ ይሆናል።
