የሩሲያው ፕሬዝዳንት የብሪክስ የመሪዎች ስብሰባ ላይ በቪዲዮ ኮንፈረንስ ባደረጉት ንግግር “የብሪክስ ሀገራት ከምድር የብስ አንድ ሦስተኛውን፤ ከፕላኔቷም ሕዝብ ግማሽ የሚጠጋውን ብቻ ሳይሆን 40 በመቶውን የዓለም ኢኮኖሚም ይይዛሉ” ብለዋል።
በሪዮ ዴ ጄኔሮ 17ኛው የብሪክስ ጉባኤ ላይ የቭላድሚር ፑቲን ቁልፍ መልዕክቶች፡-
▪️ የብሪክስ ዓለም አቀፋዊ አቋም እና ተጽዕኖ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ ነው፡፡
▪️ ብሪክስ ከግዢ ኃይል እኩልነት አንፃር እንደ ቡድን 7 ካሉ ሌሎች ስብስቦች በእጅጉ በልጧል።
▪️ የብሪክስ ሀገራት በቁልፍ ዘርፎች ትብብራቸውን አጠናክረው ቀጥለዋል ደግሞም ትልቅ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና የሰው ኃይል አቅም አላቸው፡፡
▪️ የብሪክስ ሀገራት በንግድ ልውውጥ የብሔራዊ ገንዘቦች አጠቃቀም እያደገ ነው፤ ሊቀጥል ይገባል፡፡
▪️ ብሪክስ በደቡቡ እና ምስራቃዊው ዓለም ውስጥ ብዙ መስል አስተሳሰብ ያላቸው ሀገሮች አሉት፡፡
▪️ የሊበራል ዓለም አቀፍ ሥራዓት ጊዜ ያለፈበት እየሆነ መጥቷል፡፡
▪️ የተዘዋዋሪ ካፒታል ኢንቨስትመንቶች መጠን በብሪክስ ስልቶች የማሳደግ ተግባር አስቸኳይ ነው፡፡
▪️ ብሪክስ የእህል ገበያ፣ ቋሚ የሎጂስቲክስ መድረክ እና የስፖርት የትብብር መርሃ ግብር የመፍጠር ሂደትን እየተፋጠነ ነው፡፡
▪️ ብራዚል እንደ ብሪክስ ሊቀመንበርነቷ ባለፈው ዓመት በሩሲያ የቀረበውን ውጥኖች አስቀጥላለጭ
▪️ ለጉባኤው የተዘጋጀው የመጨረሻ መግለጫ ለጥምረቱ የጋራ ሥራ ጥሩ መሠረት ይጥላል፡፡
