የገቢዎች ሚኒስቴር ኤክሳይዝ ታክስ የሚከፈልባቸውን እንደ ቢራ፣ የለስላሳ መጠጦች እና የትምባሆ ውጤቶች የሚያመርቱ ፋብሪካዎችን የማምረትና የጭነት እንቅስቃሴ በቀጥታ ለመቆጣጠር ከፍተኛ ጥራት ያላቸውን ካሜራዎች የመትከል ሥራ ጀምሯል።
የአዲሱ እርምጃዎች ቁልፍ ጉዳዮች፦
⚡️ የመመሪያ ቁጥር 1079/2025 ድንጋጌምርቶች ላይ የሚለጠፉ አካላዊ ማህተሞች ወይም ዲጂታል ኮዶች እንዲኖሩ የሚያስገድድ ሲሆን ሚኒስቴሩ በዲጂታል መንገድ ከሩቅ ሆኖ ምርቶችን እንዲቆጣጠር ሥልጣን ይሰጣል።
⚡️ መንግሥት ለዚህ የዲጂታል ቁጥጥር ሥራ 300 ሚሊዮን ብር የመደበ ሲሆን ፋብሪካዎች ቢያንስ ሁለት ካሜራዎችን በራሳቸው ወጪ እንዲተክሉ ተደርጓል።
⚡️ የካሜራ ገጠማው በየፋብሪካው የማምረቻ መስመሮች፣ የማሸጊያ ቦታዎች እና የእቃ መጫኛ ክፍሎች ላይ ትክክለኛ ቁጥጥር በማድረግ ምርት የመሸሸግ እና የታክስ ስወራ ክፍተቶችን ለመዝጋት ያለመ ነው።
