የታክስ ስወራን ለመግታት በቢራ እና በለስላሳ መጠጦች ፋብሪካዎች ላይ የካሜራ ቁጥጥር ተጀመረ

Date:

የገቢዎች ሚኒስቴር ኤክሳይዝ ታክስ የሚከፈልባቸውን እንደ ቢራ፣ የለስላሳ መጠጦች እና የትምባሆ ውጤቶች የሚያመርቱ ፋብሪካዎችን የማምረትና የጭነት እንቅስቃሴ በቀጥታ ለመቆጣጠር ከፍተኛ ጥራት ያላቸውን ካሜራዎች የመትከል ሥራ ጀምሯል።

የአዲሱ እርምጃዎች ቁልፍ ጉዳዮች፦

⚡️ የመመሪያ ቁጥር 1079/2025 ድንጋጌምርቶች ላይ የሚለጠፉ አካላዊ ማህተሞች ወይም ዲጂታል ኮዶች እንዲኖሩ የሚያስገድድ ሲሆን ሚኒስቴሩ በዲጂታል መንገድ ከሩቅ ሆኖ ምርቶችን እንዲቆጣጠር ሥልጣን ይሰጣል።

⚡️ መንግሥት ለዚህ የዲጂታል ቁጥጥር ሥራ 300 ሚሊዮን ብር የመደበ ሲሆን ፋብሪካዎች ቢያንስ ሁለት ካሜራዎችን በራሳቸው ወጪ እንዲተክሉ ተደርጓል።

⚡️ የካሜራ ገጠማው በየፋብሪካው የማምረቻ መስመሮች፣ የማሸጊያ ቦታዎች እና የእቃ መጫኛ ክፍሎች ላይ ትክክለኛ ቁጥጥር በማድረግ ምርት የመሸሸግ እና የታክስ ስወራ ክፍተቶችን ለመዝጋት ያለመ ነው።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ኢራን የአሜሪካን የጦር መርከቦች ዒላማ የማድረግ አቅም እንዳላት ገለጸች

ኢራን የአሜሪካን የጦር መርከቦች ዒላማ የማድረግ አቅም እንዳላት የአገሪቱ...

ከትግራይ ዩኒቨርሲቲ ታጣቂዎች ካልወጡ ተማሪ አንመድብም

ትምህርት ሚኒስቴር በትግራይ ክልል የሚገኙ መቐለ፣ አክሱም፣ አዲግራት እና...

ኢራን አሜሪካ የጣለችባት ዕገዳ የበለጠ የሚጎዳው ዋሽንግተንን ነው አለች

አሜሪካ በኢራን ላይ የጣለችው የኢኮኖሚ እና የባሕር እንቅስቃሴ እገዳ...

ግብጻዊቷ የቴሌቪዥን አዘጋጅ በዕፅ ዝውውር ወንጀል የሞት ፍርድ ተወሰነባት

የካይሮ የወንጀል ችሎት፤ ዕውቋን የቴሌቪዥን ፕሮግራም አዘጋጅ ሳራ ካሊፋን...