የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከብሪክስ ፖሊሲዎች ጎን ሆነው የአሜሪካንን ጥቅም የሚፃረሩ ሀገራት ተጨማሪ የ10 በመቶ ታሪፍ እንደሚጣልባቸው አስጠንቅቀዋል።
ትራምፕ የአገራትን አለም አቀፍ ደረጃ ለማሳደግ እና አሜሪካን እና ምዕራባዊ አውሮፓን ለመቃወም የተነደፈውን ቻይና፣ ሩሲያ እና ህንድን የሚያጠቃልለውን Brics የተባለውን ድርጅት ሲነቅፉ ቆይተዋል።
ትራምፕ “ከ BRICS ፀረ-አሜሪካዊ ፖሊሲዎች ጋር የሚጣጣም ማንኛውም ሀገር ተጨማሪ 10 በመቶ ታሪፍ ይጣልበታል ። ከዚህ ፖሊሲ ምንም ልዩ ሁኔታዎች አይኖሩም” ብለዋል ።
