የቻይና አምባሳደር ከኦሞቲክ መስራች አቶ ኢያሱ ጋር ተወያዮ

Date:

በኢትዮጵያ የቻይና አምባሳደር ቺን ሀይ የተመራ የኢንቨስተሮች ልዑክ ከኦሞቲክ ግሩፕ መስራችና ባለቤት እንዲሁም ከአፍሪካ ቦክስ ኮንፌደሬሽን ፕረዝዳንት ከሆኑት አቶ ኢያሱ ወሰን ጋር ተወያዩ።

‎በቻይና አምባሳደር ቺን ሀይ የተመራው ልዑክ አርባምንጭ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ የክልል እና የዞን የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች፣ የሀገር ሽማግሌዎች እንዲሁም የሚመለከታቸው አካላት አቀባበል ያደረጉላቸው ሲሆን ከክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጋር በተለያዩ ጉዳዮች ዙሪያ የሁለትዮሽ የስራ ስምምነት ላይ ተወያይተው ተፈራርመዋል።


ከልዑኩ ጋር በሆቴል፣ ቱሪዝም፣ ማዕድን፣ በግብርና እና አግሮ ፕሮሰሲንግ ኢንቨስትመንት የሁለትዮሽ ትብብር ላይ የተወያዩት አቶ ኢያሱ ወሰን ፤ ኢንቨስተሮቹ ጋር በጋራ ለማልማት ከስምምነት ደርሰዋል።

በጋሞ ዞን እና በጠቅላላው በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የሚገኙ እምቅ ሃብቶችን እና የኢንቨስትመንት ዕድሎችን ለልዑኩ ያስረዱት አቶ ኢያሱ “በርካታ ኢንቨስትመንቶች ላይ በመሰማራት አከባቢውን ማልማት እና ግዙፍ የስራ ዕድል መፍጠር እንችላለን” ሲሉም ገልፀዋል።


‎አምባሳደር ቺን ሀይ እና የቻይና ባለሀብቶቹም ከአቶ ኢያሱ ወሰን እና መሰል ባለሀብቶች ጋር መስራት የሚችሉበት የኢንቨስትመንት አማራጮች ላይ በመመያየት ፍላጎታቸውን ገልፅው በቀጣይ ጥናቶችን በማድረግ ወደ ስራ የሚገቡበትን ሁኔታ ለማመቻቸት ከስምምነት ተደርሷል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ትራምፕ ከኢራን ጋር የተስማሙባቸውን ነጥቦች ከአርብ በፊት ይፋ ሊያደርጉ ይችላሉ

የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከኢራን ጋር ጦርነቱን ለማቆም የተስማሙባቸውን...

‹‹ሃገረ ትግራይ›› በዘመናት መነፅር ሲታይ

(አጭርዳሰሳ) በወሰንሰገድ ገ/ኪዳን (ጋዜጠኛ) የመጽሐፉርዕስ፡- ሃገረ ትግራይ የመጽሐፉ ዓይነት፡-...

እንግሊዝ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ አገደች

የእንግሊዝ መንግሥት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎች...