ለንግድ ማህበረሰብ በሙሉ
ከቻይና የንግድ ድርጅቶች ጋር በጋራ መስራትን ይመለከታል
በአፍሪካ የቻይና ንግድ ምክር ቤት በኢትዮጵያ እና በቻይና ቢዝነሶች መካከል ጠንካራ ኢኮኖሚያዊ ትስስር ለመፍጠር እና የጋራ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ በማሰብ የኢትዮጵያ ኩባንያዎች ከቻይና ኢንተርፕራይዞች ጋር በትብብር ለመስራት፣ የንግድ ልዑካን እና የአጋርነት ፕሮግራሞችን ለማዘጋጀት እና ከቻይና አቻቸው ጋር የሚገናኙበትን መንገድ ለማመቻቸት የዳሰሳ ጥናት በመስራት ላይ እንደሚገኝ የቻይናው ሲሲኢሲሲ ኩባንያ ለምክር ቤቱ በመጥቀስ በዋትሳፕ እና በኢሜል በላከዉ መልእክት ፍላጎቶች እንዲሰበሰቡለት ጠይቋል፡፡
ስለሆነም ከቻይና ድርጅቶች ጋር በቀጣይ ለመስራት ፍላጎት ያላችሁ የንግድ ድርጅቶች በ https://forms.gle/4r1f6zoFdzZh2m8x9 ሊንክ በመሙላት እንዲትልኩ ወይንም ከስር የተያያዘውን ቅጽ በመሙላት እስከ ጥር 6/2018 ድረስ በኢሜይል roman@ethiopianchamber.com እንድታሳውቁን እንጠይቃለን፡፡
ከሰላምታ ጋር
የኢትዮጵያ ንግድ እና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት
