የአሜሪካ ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ክርስቶፈር ላንዳው በቢሾፍቱ በተካሄደው የኢፌዴሪ አየር ኃይል 90ኛ ዓመት ክብረ በዓል ማጠቃለያ መርሐ-ግብር ላይ ታድመዋል።
ከአሜሪካ ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ክርስቶፈር ላንዳው በተጨማሪ የአሜሪካ አፍሪካ ዕዝ አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ዳግቪን አንደርሰን፣ በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኸርቪን ማሲንጋ ተገኝተዋል።
የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ፣ የአየር ኃይል ዋና አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ይልማ መርዳሳን ጨምሮ የመከላከያ ሠራዊቱ ከፍተኛ አመራሮች ለእንግዶቹ በአየር ኃይል ግቢ አቀባበል አድርገውላቸዋል።
እንግዶቹ የኢፌዴሪ አየር ኃይል 90ኛ ዓመት ክብረ በዓልን አስመልክቶ የተዘጋጀውን የአቪዬሽን ኤክስፖ የጎበኙ ሲሆን የክብረ በዓሉ የማጠናቀቂያ ዝግጅት ላይ ታድመዋል።
