ከሄኖሲስ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኃላፊነቱ የተወሰነ መሰረታዊ ህብረት ስራ ማህበር በተገኘ ብድር ከኢትዮ ኢቪ የመኪና አስመጪ ጋር በመተባበር የአራራይ የታክሲ ዘርፍ ማህበር ለቆጠቡ አባላቶቹ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን አስረክቧል።
ሶስቱ ድርጅቶች በጋራ በመሆን ያስረከቧቸዉ መኪኖች የመጀመሪያ ዙር ሲሆን በዚህ 30 መኪኖችን ማስረከብ ችለዋል፡፡
በቀጣይ ደግሞ ለብዙሀኑ ተደራሽ ለመሆን እንደሚሰሩና የአራራይ የታክሲ ዘርፍ ማህበር አባላትን በሙሉ የመኪና ባለቤት እንዲሆኑ ስራዎች እንደሚሰሩ ተገልጿል።
መኪናቸዉን የተረከቡ የማህበሩ አባላትም ማህበራቸዉን ጨምሮ ብድሩን ላመቻቸላቸዉ ሄኖሲስ፤ መኪኖቹን ላቀረበዉ ኢትዮ ኢቪ በአጭር ጊዜ ስላስረከቧቸዉ ምስጋናቸዉን አቅርበዋል፡፡
