የአዋሽ ወልድያ ሃራ ገበያ የባቡር ፕሮጀክት በድጋሚ ጥገናዉን ሊቀጥል ነው

Date:

ኢትዮጵያን ከጅቡቲ ወደብ ጋር ያገናኛል የተባለው በቱርኩ ያፒ መርከዚ ተቋራጭ ከ10 ዓመት በፊት 1.7 ቢሊየን ዶላር የተመደበለት የአዋሽ ወልድያ ሃራ ገበያ የባቡር ፕሮጀክት ጉዳቱ ተጠንቶ ተለይቷል ተባለ።

በሰሜኑ ጦርነት ወቅት ከፍተኛ ዝርፊያ ተፈፅሞበታል የተባለው፤ ስራውም ተቋርጦ የቆየው ይህ ፕሮጀክት እንደገና ለመቀጠልም ስራ መጀመሩ ተሰምቷል።

ባቡሩ ከጦርነት እና ግጭት ባለፈ በተፈጥሮ፤ መሬት መንቀጥቀጥ ጭምር የተወሰኑ ኪሎ ሜትሮች ጉዳት እንደደረሰበት ተረድተናል።

የዚህን ፕሮጀክት ዳግም ጀምሮ ለማጠናቀቅ ጉዳቱ እንደተለየና በእቅድ እንደተያዘ የኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ ኢንጂነር ህሊና በላቸው ነግረውናል።

አዋሽ ወልዲያ ሀራ ገበያ የባቡር ንጣፍ መስመር ፕሮጀክት 375 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው ነው።

መስመሩ ሰሜን ምስራቅ ኢትዮጵያን ከማእከላዊ ኢትዮጵያ ጋር የሚያገናኝ ነው።

የአፋር፣ የአማራና የትግራይ ክልሎች ደግሞ ይኸው የባቡር ንጣፍ መስመር የሚያልፍባቸው ናቸው።

ኢትዮጵያን ከጅቡቲ ወደብ ጋር ያገናኛል የተባለው ይህ ባቡር በሰዓት 120 ኪሎ ሜትር እንዲወረወር ተደርጎ ዲዛይን የተደረገለት ነበር።

ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ…… https://www.mixcloud.com/ShegerFM/43t6/

ሸገር 102.1

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ትራምፕ የኢራን የኒውክሌር ተቋም ላይ ጥቃት ለማድረስ ዛቱ

አሜሪካ በኢራን ላይ የምታደርሰው ጥቃት 11ኛ ቀኑን ይዟል። ፕሬዝዳንት...

በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የአሜሪካ ” American Space ” ማዕከል ተመረቀ

በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቨን ማሲንጋ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የተቋቋመውን "American...

አሐዱ ባንክ ለ 8ኛ ጊዜ የደም ልገሳ መርሐ ግብር አከናወነ

አሐዱ ባንክ ሥራ የጀመረበትን 4ኛ ዓመት በማስመልከት የተለያዩ ኩነቶችን...

ዕንባ ጠባቂ ከቀረቡለት አቤቱታዎች 84% በመንግስታዊ ተቋማት ላይ የቀረቡ ናቸው

የኢትዮጵያ ህዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም በተጠናቀቀው የ2018 በጅት ዓመት...