ከ18 እና ከ20 ዓመት በታች የአፍሪካ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ዛሬ በናይጄሪያ ይጀመራል።
ኢትዮጵያ በመድረኩ በ28 አትሌቶች የምትወከል ሲሆን የልዑክ ቡድኑም ናይጄሪያ ደርሷል።
ለ5 ቀን በሚቆየው ውድድር ኢትዮጵያ ከ100 ሜትር ጀምሮ እስከ 10 ሺህ ሜትር በሁለቱም የዕድሜ ርከን የምትካፈል ይሆናል።
በሻምፒዮናው ከ43 በላይ ሀገራት ይሳተፋሉ ተብሎም ይጠበቃል።
ውድድሩ ከመጀመሩ በፊት በናይጄሪያ የአፍሪካ አትሌቲክስ ኮንፌደሬሽን ኮንግረንስ ተደርጓል።
