ፕሬዚዳንቱ ጉብኝቱ ሃገራቸው ከደቡብ ሱዳን ጋር ያላትን ግንኙነት ለማጠናከር ያለመ ነው ብለዋል።
ፕሬዚዳንት ሙሴቬኒ ወደ ጁባ ያመሩት በፕሬዚዳንት ሳልቫ ኪር ግብዣ መሆኑን የተናገሩ ሲሆን በሁለቱ ሃገራት መሃል ያለውን ግንኙነት እና ትብብር ለማጠናከር መወያየታቸውንም ተናግረዋል።
ውጥረት በቀጠለባት ደቡብ ሱዳን ኡጋንዳ ጦሯን ወደ ደቡብ ሱዳን በመላክ ለፕሬዚዳንት ሳልቫ ኪር ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች። በናስር ከተማ በተፈፀመው ጥቃትም የኬሚካል መሳሪያ ተጠቅማለች ተብላ ስትወቀስ ቆይታለች።
