የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምርጫ በሚያካሂድባቸው ቦታዎች ሁሉ እሳተፋለሁ

Date:


በዘንድሮው ሀገራዊ ምርጫ እንደሚሳተፍ ያስታወቀው የኢትዮጵያ ዜጎች ለማሕበራዊ ፍትህ ፓርቲ ኢዜማ ግንቦት 24 ይካሄዳው ተብሎ በሚጠበቀው ሀገራዊ ምርጫን አስመልክቶ ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ ሰጥቷል፡፡

ኢዜማ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ምርጫውን በሚያካሂድባቸው አካባቢዎች ሁሉ እሳተፋለሁ ያለ ሲሆን ምርጫ የዴሞክራሲ ባህል መገንቢያ መሳሪያ መሆኑን አስታዉቋል።

ፓርቲው ላለፉት አራት ዓመታት በምርጫው ንቁ ተሳትፎ ለማድረግ በዝግጅት ላይ መሆኑን አስታዉቆ የትግራይ እና የአማራ ክልልን ጨምሮ የምርጫ ቦርድ ምርጫ ለማካሄድ ባሰበባቸው ስፋራዎች ሁሉ ምርጫ ለማካሄድ ዝግጁ መሆኑን በመግለጫው አመላክቷል፡፡

በተጨማሪም ተፎካካሪ ፓርቲዎች ከስሜት ቀስቃሽ እንቅስቃሴ ታቅበው የመፍትሄ ሃሳብ በማቅረብ ምርጫውን ለምርጫ ዓላማ ብቻ እንዲጠቀሙ እና መንግሥትን ጨምሮ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ምርጫው ተጀምሮ እስኪጠናቀቅ የሚጠበቅባቸውን ኃላፊነት እንዲወጡ ጥሪ አቅርቧል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንኳን ለብርሃነ ጥምቀቱ አደረሳችሁ፤ አደረሰን

ሰማያት ተከፈቱ ፣ ምስጢርም ተገለጠ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ዘመዷ ቅድስት...

አባቴ ለእኔ አባት ብቻ አልነበረም፤ ለእናቴ ታማኝ ባል፣ ለሁላችንም ደግሞ የደስታ ምንጭ ነበር

"አባዬ… ዛሬ ላለሁበት ማንነት መሰረት የሆንከኝ አንተ ነህ!" ​የአርቲስት...

የአንበሶቹ ትንሳኤ፦ የዳካር እንባ እና የቴራንጋ ድል

​በዳካር ሰማይ ስር ዛሬ ጨረቃ አልወጣችም፤ ይልቁንም በሚሊዮን የሚቆጠሩ...

የጥምቀት በዓል በመላ ሀገሪቱ በድምቀት እየተከበረ ነው

የጥምቀት በዓል በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን እና በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት...