የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለስልጣን የሰነድ ማስረከቢያ ጊዜን አራዘመ

Date:

የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለስልጣን በህዝብ የተያዙ ኩባንያዎች አስፈላጊ ሰነዶችን እና መረጃዎችን እንዲያቀርቡ የተሰጠውን ቀነ-ገደብ ለአንድ ወር ማራዘሙን አስታወቀ።

ባለስልጣኑ ቀደም ሲል ባወጣው መግለጫ መሠረት፣ ኩባንያዎቹ እስከ መጋቢት 4 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ ሰነዶችንና መረጃዎችን እንዲያቀርቡ አሳስቦ ነበር። ነገር ግን፣ ከኩባንያዎቹ የቀረቡትን ጥያቄዎች እና ተጨማሪ መረጃዎችን ለመቀበል እንዲቻል የጊዜ ገደቡ እስከ ሚያዚያ 1 ቀን 2017 ዓ.ም. ድረስ ተራዝሟል።

ይህ ማራዘሚያ አስፈላጊውን መረጃ እስካሁን ላላቀረቡ ኩባንያናት የመጨረሻ እድል እንደሆነ የተገለጸ ሲሆን፣ ባለስልጣኑ ኩባንያናቱ የተራዘመውን ጊዜ በአግባቡ በመጠቀም አስፈላጊ ሰነዶችንና መረጃዎችን እንዲያቀርቡ አሳስቧል።

ማራዘሚያው ከ50 በላይ የአክሲዮን ባለቤቶች ያሏቸው እና በአሁኑ ወቅት አክሲዮኖችን ለህዝብ ሽያጭ በማቅረብ ላይ ያሉ ኩባንያዎችን ይመለከታል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከባድ ሙስና የተከሰሱትን 4 ተከሳሾችን፤ ፖሊስ ፍርድ ቤት ማቅረብ ሳይችል ቀረ

በከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመስርቶባቸው በፖሊስ የ'ይፈለጋሉ" ማስታወቂያ የወጣባቸው...

ስለመካከለኛው ምስራቅ አዲስ ውጥረት እስካሁን የታወቁ ጉዳዮች

🔸 ትላንት ምሽት ከኢራን ግዛት የተተኮሰ የሮኬት ጥቃት በሰሜናዊ...

የወንጀል ሥነ-ሥርዓትና ማስረጃ ሕጉ በጋዜጣ እስኪታተም ረቂቅ ሰነዶችን ከመጠቀም እንዲቆጠብ የፍትሕ ሚኒስቴር አሳሰበ

የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. የፍትሕ ሚኒስቴር አዲሱ የወንጀል ሕግ ሥነ-ሥርዓትና ማስረጃ ሕግ...

ፔንታጎን የእስራኤል ስለላ እንደሚያሳስበው ተገለጸ

ከቅርብ ሳምንታት ወዲህ ፔንታጎን እስራኤል ከፍተኛ ልዑኮችን ጨምሮ የአሜሪካ...