የኢትዮጵያ የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ ”ንዋይ” የተሰኘ መተግበሪያን ይፋ አደረገ

Date:

የኢትዮጵያ የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ በመላ ሀገሪቱ የሚገኙ ዜጎች በካፒታል ገበያ ላይ በቀላሉ ኢንቨስት እንዲያደርጉ የሚያስችለውን “ንዋይ” የተሰኘ የመጀመሪያውን የድረ-ገጽና የሞባይል ግብይት መተግበሪያ በይፋ ማስጀመሩን አስታወቀ።

ዛሬ ይፋ የተደረገው ይህ መተግበሪያ፣ ገበያው ከዓለም አቀፉ የቴክኖሎጂ አቅራቢ “ኢንፎቴክ ፕራይቬት ሊሚትድ” ጋር በመተባበር ያበለጸገው እንደሆነ ተጠቁሟል።

መተግበሪያው ደንበኞችን በቀላሉ ለመመዝገብ፣ የሽያጭና ግዢ ትዕዛዞችን ለማስተላለፍ እንዲሁም የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴዎችን በየሰዓቱ ለመከታተል የሚያስችሉ ዘመናዊ አሰራሮችን አካትቷል።

የገበያው ዋና ሥራ አስፈጻሚ ጥላሁን እስማኤል ካሰሁን (ዶ/ር) በመድረኩ ላይ እንደገለጹት፣ “ንዋይ” መተግበሪያ የሀብት ተደራሽነትን ዲሞክራሲያዊ በማድረግ እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ባሉበት ቦታ ሆኖ በሀገሪቱ የኢኮኖሚ ዕድገት ውስጥ ተሳታፊ እንዲሆን ዕድል ይፈጥራል።

መተግበሪያው ጠንካራ የደህንነት ሥርዓት (KYC) ያለው በመሆኑ፣ የኢንቨስተሮችን ጥበቃ የሚያረጋግጥና በገበያው ላይ ያለውን እምነት የሚያሳድግ መሆኑ ተገልጿል። ይህም በኢትዮጵያ የፋይናንስ ሥነ-ምህዳር ላይ ከፍተኛ ለውጥ ያመጣል ተብሎ ይጠበቃል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አርሰናል ከቦርንማውዝ በጉጉት የሚጠበቅ ጨዋታ

በ32ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ዛሬ ቀን...

በአሜሪካ እና ኢራን ድርድር ላይ የሚነሱ አራት ቁልፍ ጥያቄ

በፓኪስታን የሚደረገው የአሜሪካ እና የኢራን ድርድር እየተጠበበፓኪስታን ነገር ግን...

መንገዳችን ረጅም፣ ጉዟችን ፈታኝ መሆኑን እናውቃለን

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለኢየሱስ ክርስቶስ የትንሣኤ በዓል...

የተመድ ዋና ጸሐፊ ኢራን እና አሜሪካ “በቅን ልቦና” ወደ ድርድሩ እንዲገቡ ጠየቁ

የተባበሩት መንግሥታት ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ አሜሪካ እና ኢራን...