የተባበሩት መንግስታት ድርጅት (ተ.መ.ድ) ኤጀንሲዎች ዛሬ ባወጡት ሪፖርት፣ ከእርግዝና እና ከወሊድ ጋር በተያያዙ ምክንያቶች የሚሞቱ እናቶች ቁጥር በዓለም አቀፍ ደረጃ በ40 በመቶ ቢቀንስም፣ እየተካሄደ ያለው የዓለም አቀፍ የገንዘብ ድጋፍ ቅነሳ ይህን እድገት አደጋ ላይ ጥሏል።
ሪፖርቱ ከ2016 ጀምሮ የእድገቱ ፍጥነት መቀዛቀዙንና በ2023 ብቻ 260,000 የሚገመቱ ሴቶች መሞታቸውን ያሳያል።
በተለይም በሰብአዊ ቀውሶች ውስጥ የሚገኙ ነፍሰ ጡር ሴቶች ከፍተኛ አደጋ ላይ መሆናቸው ተገልጿል።
የተ.መ.ድ ኤጀንሲዎች የእናቶችን ህይወት ለመታደግ የሚያስፈልገውን ድጋፍ በአስቸኳይ እንዲጨምር ጥሪ እያቀረቡ እንደሚገኙ ተጠቁሟል።
