የጋምቤላ ክልል በጸጥታ ችግር የምርጫ ቦርድ የጊዜ ሰሌዳ ማሻሻያ እንዲደረግበት ጠየቀ

Date:

የ7ተኛው ጠቅላላ ምርጫ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም እንደሚከናወን መገለጹ የሚታወስ ሲሆን፣ በአንዳንድ አካባቢዎች በቅድመ-ምርጫ ወቅት መከናወን ያለባቸው ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑ ተገልጿል።

ሆኖም በጋምቤላ ክልል ለሚካሄደው ምርጫ የጸጥታው ሁኔታ እክል እንዳይፈጥር ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚፈልግ የክልሉ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት አስታውቋል።

የክልሉ የጋራ ምክር ቤት አባል እንዲሁም በኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት የአቅም ግንባታ ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ አቶ ሳይመን ቱት ምርጫው አስፈላጊ መሆኑን ገልጸው፤

በክልሉ ምክር ቤት ስር አምስት ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች እንደሚገኙና አራቱ በንቃት እየተሳተፉ መሆኑን አስታውቀዋል። የፖለቲካ ፓርቲዎቹም በተናጠል እያከናወኑዋቸው ያሉ ተግባራት እንዳሉ ጠቁመዋል።

ምንም እንኳን ፓርቲዎቹ ለምርጫው ዝግጅት ለማድረግ ጥረት ላይ ቢሆኑም፣ በክልሉ ያለው የጸጥታ ችግር ከፍተኛ ስጋት እንደፈጠረባቸው አቶ ሳይመን ቱት ገልጸዋል።

በመሆኑም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የ7ተኛውን ጠቅላላ ምርጫ የጊዜ ሰሌዳ ይፋ ቢያደርግም፣ በጸጥታ ችግር ውስጥ ለሚገኙ ክልሎች ጊዜው እንዲራዘም ጠይቀዋል።

በጉዳዩ ዙሪያ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምላሽ ለማግኘት ያደረግነው ጥረት ለጊዜው አልተሳካም።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የጣሊያን ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ ሜሎኒ አዲስ አበባ ገቡ

ጠቅላይ ሚኒስትሯ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ ጠቅላይ...

የቴሌኮም ኦፕሬተሮች የ5 በመቶ የአደጋ ሥጋት ምላሽ ፈንድ ክፍያን ተግባራዊ ማድረግ ጀመሩ

በኢትዮጵያ የሚንቀሳቀሱት ሁለቱም የቴሌኮም ኦፕሬተሮች ማለትም ኢትዮ ቴሌኮም እና...

የአውሮፓ ፓርላማ ፕሬዚዳንት ለኢራን ህዝብ – “እኛ ከእናንተ ጋር ነን”

የአውሮፓ ፓርላማ ፕሬዝዳንት ሮቤርታ ሜትሶላ፥ የኢራን መንግስት በተቃዋሚዎች ላይ...

አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ ውክልና ሊኖራት ይገባል

በተባበሩት መንግስታት የፀጥታው ምክር ቤት አፍሪካ ቋሚ ውክልና...