የ24ተኛ ሳምንት መርሐ ግብሮች አርሰናል፣ቼልሲ እና ሊቨርፑል ተጋጣሚዎቻቹውን አሸነፉ

Date:

የሊጉ መሪ አርሰናል ሊድስ ዩናይትድን 4ለ0 በማሸነፍ መሪነቱን አጠናክሯል።

የአርሰናልን ግቦች ዙቢሜንዲ ፤ ቪክቶር ዮኬሬሽ ፤ ጋብሬል ጄሱስ እና ዳርሎው በራሱ መረብ ላይ አስቆጥሯል። ጋብሬል ጄሱስ ባለፉት አራት ጨዋታዎች ሶስት ግቦችን አስቆጥሯል።

ቼልሲ ዌስትሀም ዩናይትድን 3ለ2 በሆነ ውጤት አሸነፍ።

ዌስትሀም ዩናይትድ በጃሮድ ቦውን እና ሰመርቪሌ ሁለት ግቦች ጨዋታውን 2ለ0 ሲመራ ቢቆይም  ጇ ፔድሮ ፤ ማርክ ኩኩሬላ እና ኢንዞ ፈርናንዴዘ ከእረፍት በኋላ  ባስቆጠሯቸው ሶስት ግቦች ቼልሲ አሸንፎ ወጥቷል።

በአሰልጣኝ ሊያም ሮሴንየር የሚመራው ቼልሲ አምስተኛ ተከታታይ ድሉን ማሳካት ችሏል።

ሊቨርፑል ከኒውካስል ዩናይትድ ጋር ያደርገውን ጨዋታ 4ለ1 በሆነ ውጤት ማሸነፍ ችሏል።

የሊቨርፑልን የማሸነፊያ ግቦች ሁጎ ኤኪቲኬ ሁለት ፣ ፍሎሪያን ቨርትዝ እና ኮናቴ ከመረብ ማሳረፍ ችለዋል።

ሊቨርፑል ከአምስት የፕሪሚየር ሊግ ጨዋታዎች በኋላ ሶስት ነጥብ አሳክቷል።

ፍሎሪያን ቨርትዝ ባለፉት ስድስት ጨዋታዎች ስድስት የግብ ተሳትፎ ማድረግ ችሏል።

በሌሎች ጨዋታዎች  በርንማውዝ ዎልቭስን 2ለ0 ሲያሸንፍ ኤቨርተን ከብራይተን 1ለ1 ተለያይተዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የጣሊያን ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ ሜሎኒ አዲስ አበባ ገቡ

ጠቅላይ ሚኒስትሯ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ ጠቅላይ...

የቴሌኮም ኦፕሬተሮች የ5 በመቶ የአደጋ ሥጋት ምላሽ ፈንድ ክፍያን ተግባራዊ ማድረግ ጀመሩ

በኢትዮጵያ የሚንቀሳቀሱት ሁለቱም የቴሌኮም ኦፕሬተሮች ማለትም ኢትዮ ቴሌኮም እና...

የአውሮፓ ፓርላማ ፕሬዚዳንት ለኢራን ህዝብ – “እኛ ከእናንተ ጋር ነን”

የአውሮፓ ፓርላማ ፕሬዝዳንት ሮቤርታ ሜትሶላ፥ የኢራን መንግስት በተቃዋሚዎች ላይ...

አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ ውክልና ሊኖራት ይገባል

በተባበሩት መንግስታት የፀጥታው ምክር ቤት አፍሪካ ቋሚ ውክልና...