ዩኒሊቨር ኢትዮጵያ አቶ ነሲቡን አዲስ ሥራ አስኪያጅ አድርጎ ሾመ

Date:

ዩኒሊቨር ኢትዮጵያ አቶ ነሲቡ ተመስገንን አዲስ ሥራ አስኪያጅ አድርጎ ከመጋቢት 23 ቀን 2017 ጀምሮ እንዲያገለግሉ መሾሙን አስታወቀ። 18 ዓመታትን ያስቆጠረ የሥራ ልምድ ያላቸው አቶ ነሲቡ፣ ከዚህ ውስጥ ግማሽ ያህሉን በዩኒሊቨር ኢትዮጵያ በተለያዩ የኃላፊነት ቦታዎች ላይ አገልግለዋል።

ነሲቡ በዩኒሊቨር ኢትዮጵያ በነበራቸው ቆይታ የድርጅቱን ሽያጭ እና የገበያ አቋም በከፍተኛ ደረጃ በማሳደግ ቁልፍ ሚና መጫወታቸውን ኩባንያው ገልጿል ።

“ምርታማነትን ያማከለ እድገት፣ የሰው ኃይል ማብቃት እና የላቀ አፈጻጸም ቅድሚያ ትኩረቴ ናቸው” ያሉት አቶ ነሲቡ፣ “የዩኒሊቨርን እሴቶች እና ባህሪያት በመጠበቅ ተገቢውን የቁጥጥር እና የአስተዳደር ስርዓት በመዘርጋት ይህን እውን ለማድረግ ቁርጠኛ ነኝ” ብለዋል።

ከኩባንያዉ ለካፒታል በተላከዉ መግለጫ አቶ ነሲቡ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በማርኬቲንግ ማኔጅመንት የመጀመሪያና ሁለተኛ ዲግሪያቸውን የተማሩ ሲሆን፣ በዩኒሊቨር የሚሰጠውን የአፍሪካ ሊደርሽፕ አክስሌረተር ፕሮግራምንም አጠናቀዋል።

መቀመጫው በእንግሊዝ ሀገር የሆነው የአለም አቀፉ ዩኒሊቨር በኢትዮጵያም ላለፉት ስምንት ዓመታት እንደ ላይፍቦይ፤ ኦሞ እና ክኖር የመሳሰሉ የግልና የጋራ ንጽህና መጠበቁያዎች እንዲሁም ምግብ ነክ ምርቶችን እያቀረበ ለተጠቃሚዎች የሚያቀርብ አምራች ድርጅት መሆኑ ይህ ።

CapitalNews

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ግዮን መጽሔት ዛሬ ቅዳሜ ግንቦት 1 2018 ዓ.ም ገበያ ላይ ውሏል !!!

በኢትዮጵያ ነፃ ኘሬስ ከ25 ዓመት በላይአገልግለናል !!! -የአርበኞች አደራና የትውልዱ...

ከሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ የተላለፈ ጥሪ

በክልላችን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እያደገ የመጣው የተሳሳተ ስሌት የወለደው...

በሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ ላይ በከባድ መሳሪያዎች የታገዘ  የተኩስ ልውውጥ ተካሄደ

ለዓለም የንግድ ሰንሰለት እጅግ ስትራቴጂካዊ በሆነው የሆርሙዝ ባህረ ወሽመጥ...

የሲ.ኤን.ኤን መስራች ቴድ ተርነር ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

የዓለማችን ግዙፍ የዜና አውታር ሲኤንኤን መስራች ቴድ ተርነር በ87...