ዩኒሊቨር ኢትዮጵያ አቶ ነሲቡ ተመስገንን አዲስ ሥራ አስኪያጅ አድርጎ ከመጋቢት 23 ቀን 2017 ጀምሮ እንዲያገለግሉ መሾሙን አስታወቀ። 18 ዓመታትን ያስቆጠረ የሥራ ልምድ ያላቸው አቶ ነሲቡ፣ ከዚህ ውስጥ ግማሽ ያህሉን በዩኒሊቨር ኢትዮጵያ በተለያዩ የኃላፊነት ቦታዎች ላይ አገልግለዋል።
ነሲቡ በዩኒሊቨር ኢትዮጵያ በነበራቸው ቆይታ የድርጅቱን ሽያጭ እና የገበያ አቋም በከፍተኛ ደረጃ በማሳደግ ቁልፍ ሚና መጫወታቸውን ኩባንያው ገልጿል ።
“ምርታማነትን ያማከለ እድገት፣ የሰው ኃይል ማብቃት እና የላቀ አፈጻጸም ቅድሚያ ትኩረቴ ናቸው” ያሉት አቶ ነሲቡ፣ “የዩኒሊቨርን እሴቶች እና ባህሪያት በመጠበቅ ተገቢውን የቁጥጥር እና የአስተዳደር ስርዓት በመዘርጋት ይህን እውን ለማድረግ ቁርጠኛ ነኝ” ብለዋል።
ከኩባንያዉ ለካፒታል በተላከዉ መግለጫ አቶ ነሲቡ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በማርኬቲንግ ማኔጅመንት የመጀመሪያና ሁለተኛ ዲግሪያቸውን የተማሩ ሲሆን፣ በዩኒሊቨር የሚሰጠውን የአፍሪካ ሊደርሽፕ አክስሌረተር ፕሮግራምንም አጠናቀዋል።
መቀመጫው በእንግሊዝ ሀገር የሆነው የአለም አቀፉ ዩኒሊቨር በኢትዮጵያም ላለፉት ስምንት ዓመታት እንደ ላይፍቦይ፤ ኦሞ እና ክኖር የመሳሰሉ የግልና የጋራ ንጽህና መጠበቁያዎች እንዲሁም ምግብ ነክ ምርቶችን እያቀረበ ለተጠቃሚዎች የሚያቀርብ አምራች ድርጅት መሆኑ ይህ ።
CapitalNews
