ዩ ኤስ ኤ አይ ዲን ወደ ነበረበት እንዲመለስ ፍርድ ቤት ወሰነ

Date:

አንድ የአሜሪካ ፌደራል ፍርድ ቤት፣ የፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳድር የአሜሪካ ዓለማቀፍ ተራድዖ ድርጅትን (ዩ ኤስ ኤ አይ ዲን) ወደነበረበት እንዲመልስ ትዕዛዝ መስጠቱን ዓለማቀፍ የዜና ምንጮች ዘግበዋል።

ፍርድ ቤቱ፣ ዩ ኤስ ኤ አይ ዲ በጥድፊያ እንዲፈርስ የተደረገበት መንገድ የአሜሪካ ሕገመንግሥቱን በብዙ መንገድ ጥሷል ሊባል የሚችል ነው ማለቱን ዘገባዎቹ ጠቅሰዋል። ዩ ኤስ ኤ አይ ዲን የማፈረስ ወይም መልሶ የማዋቀር ሥልጣን የሕግ አውጭው ምክር ቤት ብቻ ሥልጣን እንደኾነ ፍርድ ቤቱ ጠቅሷል ተብሏል።

የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚንስትር ማርኮ ሩቢዮ፣ ከድርጅቱ 83 በመቶ ሥራዎች ሙሉ በሙሉ እንደታጠፉና ቀሪዎቹ በውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤቱ ሥር መጠቃለላቸውን ከሳምንት በፊት መግለጣቸው አይዘነጋም።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የጣሊያን የመከላከያ ስምምነቶችና የፖለቲካዊ ድጋፎች

በመካከለኛው ምስራቅ እየተባባሰ የመጣውን የጸጥታ ስጋት ተከትሎ፣ ጣሊያን ለባህረ...

የኢትዮጵያ የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ ”ንዋይ” የተሰኘ መተግበሪያን ይፋ አደረገ

የኢትዮጵያ የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ በመላ ሀገሪቱ የሚገኙ ዜጎች...

የነዳጅ እጥረት አሽከርካሪዎችን ለከፋ እንግልት እየዳረገ ነው

በአዲስ አበባ እና በልዩ ልዩ የክልል ከተሞች የሚስተዋለው የነዳጅ...

ሼክ ኢብራሂም ቱፋ በኢራን ኤምባሲ በመገኘት ሀዘናቸውን ገለጹ

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሼክ ኢብራሂም...