አንድ የአሜሪካ ፌደራል ፍርድ ቤት፣ የፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳድር የአሜሪካ ዓለማቀፍ ተራድዖ ድርጅትን (ዩ ኤስ ኤ አይ ዲን) ወደነበረበት እንዲመልስ ትዕዛዝ መስጠቱን ዓለማቀፍ የዜና ምንጮች ዘግበዋል።
ፍርድ ቤቱ፣ ዩ ኤስ ኤ አይ ዲ በጥድፊያ እንዲፈርስ የተደረገበት መንገድ የአሜሪካ ሕገመንግሥቱን በብዙ መንገድ ጥሷል ሊባል የሚችል ነው ማለቱን ዘገባዎቹ ጠቅሰዋል። ዩ ኤስ ኤ አይ ዲን የማፈረስ ወይም መልሶ የማዋቀር ሥልጣን የሕግ አውጭው ምክር ቤት ብቻ ሥልጣን እንደኾነ ፍርድ ቤቱ ጠቅሷል ተብሏል።
የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚንስትር ማርኮ ሩቢዮ፣ ከድርጅቱ 83 በመቶ ሥራዎች ሙሉ በሙሉ እንደታጠፉና ቀሪዎቹ በውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤቱ ሥር መጠቃለላቸውን ከሳምንት በፊት መግለጣቸው አይዘነጋም።
