አፍሪካ ከድህነት እና ኋላቀርነት ለመውጣት “ጥሬ ዕቃ ወደ ውጭ መላክ ማቆም አለባት” ሲሉ የአፍሪካ ልማት ባንክ ፕሬዝዳንት አሳሰቡ

Date:

የአፍሪካ ልማት ባንክ ፕሬዝዳንት ዶክተር አኪንዉሚ አዴሲና አፍሪካ ከድህነት እና ኋላቀርነት ለመውጣት ከፈለገች ጥሬ ዕቃዎችን ወደ ውጭ መላክ ማቆም አለባት ሲሉ አሳስበዋል።

አዴሲና ሐሙስ ዕለት በ ኤክ ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት አፍሪካ ያልተዘጋጁ ምርቶችን ከማቅረብ ወደ ተመረቱ እና ተጨማሪ እሴት ያላቸውን እቃዎች አምራችነት መሸጋገር እጅግ አስፈላጊ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል።

“አፍሪካ ጥሬ ዕቃዎቿን ወደ ውጭ መላክ ማቆም አለባት። ጥሬ ዕቃዎችን ወደ ውጭ መላክ የድህነት በር ነው። ተጨማሪ እሴት ያላቸውን ምርቶች ወደ ውጭ መላክ ደግሞ ወደ ሀብት የሚያደርስ አውራ ጎዳና ነው” ሲሉ ጽፈዋል።

እንደ አሜሪካ የንግድ ተወካይ ቢሮ እና ሌሎች ዓለም አቀፍ ተቋማት መረጃዎች እንደሚያሳዩት አፍሪካ ከዓለም የማኑፋክቸሪንግ ምርት ውስጥ ከሁለት በመቶ በታች ብቻ ነው የምትይዘው።

ይህ ሁኔታ አፍሪካ በግብርና እና በማዕድን ዘርፎች ከፍተኛ የተፈጥሮ ሀብት ባለቤት ብትሆንም በዓለም ኢኮኖሚ ውስጥ ያላት ሚና አነስተኛ እንዲሆን ምክንያት ሆኗል።

ፕሬዝዳንት አዴሲና አፍሪካ ጥሬ ዕቃዎችን በማቀነባበር የራሷን ኢንዱስትሪዎች በማሳደግ ለዜጎቿ የስራ እድል መፍጠር እና የውጭ ምንዛሬ ገቢዋን ማሳደግ እንደምትችል አስረድተዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምርጫ በሚያካሂድባቸው ቦታዎች ሁሉ እሳተፋለሁ

በዘንድሮው ሀገራዊ ምርጫ እንደሚሳተፍ ያስታወቀው የኢትዮጵያ ዜጎች ለማሕበራዊ ፍትህ...

በሲዳማ ክልል ከ62% በመቶ በላይ የሚታረሰው መሬት በአሲዳማነት የተጎዳ ነዉ

በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ የሚታየው የምርታማነት ማነቆ በዋናነት የመሬት አሲዳማነት...

የኢትዮጵያ እዳ እና ሃብት አስተዳደር ኮርፖሬሽን የሥራ ኃላፊዎች ስብሰባ ሳይገኙ ቀሩ

የመንግስት ልማት ድርጅቶች ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የኢትዮጵያ እዳ እና...

የኢትዮጵያ እና ሕንድ የቆየ ዲፕሎማሲዊ ግንኙነት

የኢትዮጵያ እና ሕንድ የቆየ ዲፕሎማሲዊ ግንኙነት የአፍሪካ-ሕንድ...