በዲጅታል እቁብ የሚታወቀው አብሮነት ሀላፊነቱ የተወሰነ መሰረታዊ ቁጠባና ብድር ህብረት ስራ ማህበር ለሰራተኞቹ የእውቅና እና የሽልማት መርሀ ግብር አካሂዷል።
ድርጅቱ ለበርካታ ዓመታት በተለይም በአካል ጉዳተኞች ዙሪያ በስፋት የሰራውንና እየሰራ ለሚገኘው ለጋዜጠኛ ተስፋየ ገ/ማርያም የመኪና ሽልማት አበርክቷል።
ጋዜጠኛ ተስፋየ ገ/ማርያም የአይቻልም መንፈስን በመርታት በስራዎቹ ብዙዎችን በማሳመን በተለይም ለአካል ጉዳተኞች መከታ ሆኖ ለዘመናት መቆየቱን በመናገር፤ ሽልማቱ ለሁሉም አካል ጉዳተኞች መታሰቢያ ይሁንልኝ ብሏል።
የጋዜጠኛ ተስፋየ ገ/ማርያም የዘመናት ልፋት በአብሮነት ሀላፊነቱ የተወሰነ መሰረታዊ ቁጠባና ብድር ህብረት ስራ ማህበር እውቅና አግኝቶ የመኪና ሽልማት ተበርክቶለታል።
