በኢትዮጵያ ቴሌቪዠን የሚድያ ዳሰሳ የሚል ፕሮግራም በማዘጋጀት የሚታወቀው ጋዜጠኛ ታደሰ ሚዛን ከዚህ ኣለም በሞት ተለይቷል።
ታደሰ በትግራይ ውቕሮ ከተማ በ1963 ዓም ተወልዶ፣ ሃምሌ 2 2017 ዓም ባደረበት ድንገተኛ ህመም ከዚህ አለም በሞት ተለይቷል።
ከሪፖርተርነት ጀምሮ እስከ ዳይሬክተርነት የገለገለና በትምህርትም በኢትዮጵያና በአሜሪካ በሚገኙ ዩኒቨርስቲዎች እሰከ ዶክትሬት ደረጃ ተምሯል።
አዲስ አበባ እያለ በኢትዮጵያ የልብ ህሙማን ማዕከል ኢቲቪ እያለ የልብ ቀዶ ጥገና ተደርጎለት እንደነበር ይታወሳል ።ለቤተሰቦች መፅናናትን ይስጥልን !
