ጣሊያን ለኢትዮጵያ የቡና ዘርፍ 10 ሚሊዮን ዩሮ ብድር አጸደቀች

Date:

የጣሊያን መንግስት የኢትዮጵያን የቡና ጥራትና ምርት ለማሳደግ 10 ሚሊዮን ዩሮ ብድር ማፅደቁ ተነግሯል።

ብድሩ የኢትዮጵያን ቡና አምራቾች፣ አቅራቢዎችንና ሌሎች በዘርፉ የተሰማሩ ባለድርሻ አካላትን ይረዳል መባሉን ካፒታል ለመረጃው ለመረዳት ችሏል።

ኢትዮጵያ ከፍተኛ መጠን ያለው ፕሪሚየም ጥራት ያለው ቡና ለማምረት እና የኤክስፖርት ገቢን ለማሳደግ የ15 ዓመት ስትራቴጂ እየተገበረች ቢሆንም በዘርፉ ካሉት ዋና ዋና ተግዳሮቶች መካከል አንዱ የፋይናንስ አቅርቦት ውስንነት እንደሆነ ተጠቁሟል ።

ኢትዮጵያ ባለፈው በጀት ዓመት ብቻ በቡና የወጪ ንግድ 1.43 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ያገኘች ሲሆን በዚህ በጀት ዓመት የመጀመሪያዎቹ 8 ወራት ውስጥ 157,000 ሜትሪክ ቶን ቡና በመላክ 1.3 ቢሊዮን ዶላር ገቢ መገኘቱ ታዉቋል።CapitalNews

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የአንበሶቹ ትንሳኤ፦ የዳካር እንባ እና የቴራንጋ ድል

​በዳካር ሰማይ ስር ዛሬ ጨረቃ አልወጣችም፤ ይልቁንም በሚሊዮን የሚቆጠሩ...

የጥምቀት በዓል በመላ ሀገሪቱ በድምቀት እየተከበረ ነው

የጥምቀት በዓል በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን እና በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት...

“ሎዛ ዘፀአት”እና “የሎዛ ድርሳናት”ተከታታይ ረጅም ልቦለድ መጻሕፍት ተመረቁ

በጋዜጠኛና ደራሲ መርዕድ እስጢፋኖስ የተጻፉት ሎዛ ዘፀአት(2014 ዓ.ም) እና...

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለጥምቀት በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ

እንኳን ለኢየሱስ ክርስቶስ የጥምቀት በዓል አደረሳችሁ፣ አደረሰን!! በክርስቲያኖች ዘንድ ጥምቀት...