ከተቋቋመ ሶስት አመትን በቀጣይ መስከረም 2018 የሚሞላው ባንኩ አለም አቀፍ ተቀባይነት ካለው ማስተር ካርድ ጋር የተዋዋለው ስምምነት እንዳስደሰተው ገልጿል።
በቀጣይ በ3 ዘርፎች ላይ ስምምነት እንዳደረገም የፀደይ ባንክ የዲጂታል ብራንች ባንኪንግ ምክትል ፕሬዘዳንት አቶ ቴውድሮስ ታደሰ ተናግረዋል። ኢንተርናሽናል ካርድ፤ ካርድ አኳየር፤ ኮሚኒቲ ፓስ እንደሚሰኙም ገልፀዋል።
ፀደይ ባንክ ካለው ደንበኞች አንፃር ከባንኩ ጋር መስራት መቻላችን ትልቅ ስኬት ነው ሲሉ የማስተር ካርድ የቢዝነስ ዴቨሎፕመንት ዳይሬክተር አቶ እልፍ አገድ በቀጣይ ባንኩን በሁሉም ረገድ ለመርዳት እንደሚሰሩም ገልፀዋል።
ባንኩ በሌላ በኩል ሰፖርት ኢዱኬሽን ከተሰኘ የትምህርት አስተዳደር ላይ ከሚሰራው ተቋም ጋር በጋራ የመስራት ስምምነት አከናውኗል።
የትምህርቱ ዘርፍ ላይ የሚስተዋለው ከወረቅት ጋር የተያያዘውን አሰራር ወደ ዲጂታላይዜሽን ለማዘዋወር አቅዶ ባለፋት አስር ዓመታት እየሰራ እንደሆነ የገለፁት የሰፖርት ኢዱኬሽንዋና ሥራ -አስፈፃሚ አቶ ሙልጌታ አሰፋ ናቸው።
ተቋሙ አሁን ላይ ከ 89 በላይ ትምህርት ቤቶች ጋር እየሰራም እንደሆነ ገልጿል።
ፕሮግራሙ ፀደይ ሰከላ እንደሚሰኝ የገለፁት የባንኩ ምክትል ፕሬዘዳንት አቶ ቴውድሮስ ናቸው። በሞባይል ባንኪንግ ወይም በስድስት መቶ ሰላሳ የባንኩ ቅርንጫፍ መጠቀም እንደሚቻልም ተገልጿል።
