ፌደሬሽኑ የሰላም ምክር ቤት በማቋቋም ከሰላም ሚኒስቴር ጋር እየሠራ መሆኑን ገለጸ

Date:

የኢትዮጵያ ሴቶች ፌደሬሽን የሰላም ምክር ቤት በማቋቋም ከሰላም ሚኒስቴር ጋር እየሰራ መሆኑን ለአሐዱ ገልጿል።

የፌደሬሽኑ ተቀዳሚ ፕሬዝዳንት ወ/ሮ አስካለ ለማ፤ “ችግሮች ሲኖሩ ግጭቶች ሲፈጠሩ በውይይት ለመፍታት ከማመቻቸት ጀምሮ ስራዎችን እየሠራን ነው” ብለዋል።

“እንዲሁም ችግሮች ከመፈጠራቸው በፊት የመከላከል ሥራ ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎች ይሠራሉ” ያሉ ሲሆን፤ በሰላም መደፍረስ ውስጥ ከማንም በፊት ተጎጂ የሚሆኑት ሴቶች መሆናቸውን ገልጸዋል።

በተመሳሳይም ከሰላም ጠቃሚ የሚሆኑትም ሴቶች መሆናቸውን በማንሳት፤ ሴቶችን ለሰላም ዘብ የማድረጉ ሥራ አስፈላጊ መሆኑን ተናግረዋል።

በዚህም ፌደሬሽኑ የተለያዩ ውይይቶችን ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ማድረጉን አንስተዋል።

በተያያዘም “ለሴቶች የሥራ ዕድል ለመፍጠር ከሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ጋር በጋራ በመሆን ሥራዎችን በማመቻቸት፣ የብድር አገልግሎት፣ የሥራ ቦታ እንዲያገኙ ለማድረግ እየተሠራ ነው” ብለዋል።

እንዲሁም የማህበራዊ፣ በጤና እና በትምህርት ላይ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር ትኩረት ተደርጎ እየተሠራ መሆኑን ገልጸዋል።

(አሐዱ ሬድዮ)

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከባድ ሙስና የተከሰሱትን 4 ተከሳሾችን፤ ፖሊስ ፍርድ ቤት ማቅረብ ሳይችል ቀረ

በከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመስርቶባቸው በፖሊስ የ'ይፈለጋሉ" ማስታወቂያ የወጣባቸው...

ስለመካከለኛው ምስራቅ አዲስ ውጥረት እስካሁን የታወቁ ጉዳዮች

🔸 ትላንት ምሽት ከኢራን ግዛት የተተኮሰ የሮኬት ጥቃት በሰሜናዊ...

የወንጀል ሥነ-ሥርዓትና ማስረጃ ሕጉ በጋዜጣ እስኪታተም ረቂቅ ሰነዶችን ከመጠቀም እንዲቆጠብ የፍትሕ ሚኒስቴር አሳሰበ

የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. የፍትሕ ሚኒስቴር አዲሱ የወንጀል ሕግ ሥነ-ሥርዓትና ማስረጃ ሕግ...

ፔንታጎን የእስራኤል ስለላ እንደሚያሳስበው ተገለጸ

ከቅርብ ሳምንታት ወዲህ ፔንታጎን እስራኤል ከፍተኛ ልዑኮችን ጨምሮ የአሜሪካ...