የኢትዮጵያ ካቶሊክ ጳጳሳት ጉባዔ በተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስ ሕልፈት የተሰማውን ሐዘን ገለጸ

Date:

የኢትዮጵያ ካቶሊክ ጳጳሳት ጉባዔ በተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስ ሕልፈት የተሰማውን ሐዘን ገልጿል፡፡

ጉባዔው ባስተላለፈው የሐዘን መግለጫ መልዕክት ÷ የኢትዮጵያ ካቶሊክ ቤተክርስቲያን በታላቁ አባት ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስ ሕልፈተ ሕይወት የተሰማትን ጥልቅ ሐዘን ትገልጻለች ብሏል፡፡

ተቀዳሚ ሙፍቲ የብዙዎች አባት፣ የሰላም እና የአንድነት ተምሳሌት ነበሩ፤ ሀገራችን ታላቅ አባትን አጥታለች ሲል ገልጿል፡፡

ከኢትዮጵያ ካቶሊክ ቤተክርስቲያን ጋር በተለይም በሀገራችን ሰላም እና እርቅን ለማውረድ በርካታ ሥራዎችን በጋራ እንደሰሩም አውስቷል፡፡

ጉባዔው ለቤተቦቻቸው፣ ለወዳጅ ዘመዶቻቸው፣ ለእስልምና እምነት ተከታዮች እና ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ መጽናናትን ተመኝቷል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስ ሥርዓተ ቀብር ተፈጸመ

የተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስ ሥርዓተ ቀብር ተፈጽሟል፡፡ በሥርዓተ...

የተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስ አስክሬን ሽኝት በሚሊንዬም አዳራሽ ተካሂዷል

የኢፌዴሪ ፕሬዝደንት ታየ አጽቀስላሴ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክርቤት...

ሸህ ዑመር ገነቴ!!!

እንዲህ ወደ ደገር…እንዲህ ወደ ገታ…ደግሞም ወደ ዳና፤ጫሌ ገንደጎራ፤የተሰየማችሁ፤ሰው መሆን…..ሰው...