ስቲሊ አር.ኤም.አይ ላለፉት አራት ዓመታት የፕላቲኒየም ሸልማት ተሸላሚው

Date:

የ2017 በጀት ዓመት 7ኛው የታማኝ ግብር ከፋዮች ዕውቅና እና ሽልማት በቅርቡ የተካሄደ ሲሆን 105 ግብር ከፋዮች በፕላቲየም ደረጃ፣ 245 በወርቅ ደረጃ እንዲሁም 350 ግብር ከፋዮች ደግሞ በብር ደረጃ በድምሩ 700 ግብር ከፋዮች እውቅና እና ሽልማት አግኝተዋል፡፡

በተጨማሪም ባለፉት አራት የግብር ከፋዮች እውቅና በተከታታይ የፕላቲኒየም ተሸላሚ የሆኑ 30 ግብር ከፋዮች ልዩ ተሸላሚዎች ሆነዋል፡፡

በዚሁ መርሃ-ግብር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መንግሥት ለግብር ከፋዮች ቃል በገባው መሰረት በገቢው ዘርፍ የሚስተዋሉ ሕገ-ወጥነትን ለመከላከል የተለያዩ በቴክኖሎጂ የተደገፉ አሰራሮችን እውን አድርጓል ብለዋል፡፡

በተጨማሪም ለሀገር የታመኑ ግብር ከፋዮችን ለማበረታታት በፕላቲየም ደረጃ ዕውቅና እና ሽልማት ለተበረከተላቸው ድርጅት ባለቤቶች ወይም ሥራ አስፈጻሚዎች ዓለማቀፍ ሥራቸውን ቀላል ያደርግላቸው ዘንድ ዲፕሎማቲክ ፓስፖርት እንደሚሰጣቸው መወሰኑ የሚታወቅ ነው፡፡

ስቲሊ አር.ኤም.አይ ኃላ.የተ.የግ.ማህ ከ 30ዎቹ ልዩ የፕላቲኒየም ደረጃ ተሸላሚ ዉስጥ አንዱ ሊሆን ችሏል፡፡

ከዚህም በተጨማሪም ሰባት የሴንቸሪ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ድርጅቶች በተለያየ ደረጃ ተሸላሚ ሆነዋል፡፡

ላለፉት አራት ዓመታት በታማኝነት የፕላቲኒየም ሸልማት ካገኙት 30 ልዩ ተሸላሚዎች ዉስጥ ስቲሊ አር.ኤም.አይ ኃላ.የተ.የግ.ማህ አንዱ በመሆንና መንግስት በሚሠጠዉ ማበረታቻ እና ድጋፍ ከኢትዮጵያ ውጭ በተመረጡ የአፍሪካ ሀገራት ኢንቨስት እንዲያደርግ ጥሪ እንደቀረበለት ተቋሙ አስታውቋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ኢትዮጵያ የ1 ቢሊዮን ዶላር የቦንድ ዕዳዋን ለማዋቀር ስታደርግ የነበረዉ ድርድር ያለ ስምምነት ተቋረጠ

የኢትዮጵያ መንግሥት በ2024 ዓ.ም. ዋናው ዕዳ የሚከፈልበት የአንድ ቢሊዮን...

የትግራይ ኃይል አባላት ሰልፍ ዛሬም በሌላ አቅጣጫ ቀጥለዋል

በመቐለና ዙሪያዋ የሚገኙ የትግራይ ኃይል አባላይ ትናንት ሰኞ ጥቅምት...

የምርመራ ኬዝ ስለሆነ ጥንቃቄ ያስፈልገዋል

ተማሪ ሊዛ ደሳለ የተባለች ወጣት ሰሞኑን በደሴ ከተማ “...

የቤተ ክርስቲያኗ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባዔ ዓለም አቀፍ መደበኛ ስብሰባ መካሄድ ጀመረ

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ አጠቃላይ ሰበካ...