ሽልማቱ ለሜቄዶንያ የአረጋውያን እና የአእምሮ ህሙማን መርጃ ማህበር ማስታወሻ ይሁንልኝ

Date:

የ2025 የአፍሪካ ኢምፓክት አዋርድ ሽልማትን ለሜቄዶንያ የአረጋውያን እና የአእምሮ ህሙማን መርጃ ማህበር መታወሻነት እንዲሆንለት ሰይፉ ፋንታሁን ጠይቋል፡፡

በሚዲያው ዘርፍ የዘንድሮ የ2025 የአፍሪካ ኢምፓክት አዋርድ ተሸላሚ የሆነው ታዋቂው የመገናኛ ብዙሃን ባለሞያው ሰይፉ ፋንታሁን ይህ ሽልማት ሜቄዶንያን ለማስታወስ ሊሆን እንደሚገባ አስታውቋል፡፡

በዘንድሮ የ2025 የአፍሪካ ኢምፓካት አዋርድ የአየር መንገዱ አቶ መስፍን ጣሰው፣ አትሌት መሰረት ደፋር፣ ድምፃዊ መሃሙድ አህመድ፣ ጆ ማሞ እና ሰይፉ ፋንታሁንን ተሸላሚ አድርጓል፡፡

ይህ አመታዊ የእውቅና ሽልማት ስነ ስርአት በአሜሪካና በአፍሪካ በሙያቸው ታላቅ ሥራ የሰሩ ግለሰቦችን ለማክበር የሚሰናዳ ነው።

በየአመቱ ከስፖርት፣ ከስነ ጥበብና ከስራ ፈጠራ ዘርፎች ለማህበረሰቦቻቸው ላበረከቱት አስተዋፅኦና ለለውጥ ላደረጉት የላቀ ተሳትፎ ከየዘርፉ ተመርጠው የሚሸለሙበትም መድረክ ነው።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በ7.2 በመቶ ያድጋል ተብሎ ይጠበቃል

ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (አይ ኤም ኤፍ) ለመጠናቀቅ ሁለት...

በአክሱም ዩንቨርስቲ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ በእሳት አደጋ በሚሊዮኖች የሚገመት ንብረት ወደመ

በአክሱም ዩኒቨርስቲ ጤና ሳይንስ ኮሌጅና አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል መንስኤው...

የትግራይ ኃይል አባላት ሰልፈኞች ለአራተኛ ቀን የመኪና መንገድ ዘግተዋል

ጥቅምት 6/2018 ዓ.ም የትግራይ ምስራቃዊ ዞን ዋና ከተማ ወደ...