ቃል አቀባይዋ ዩክሬን የአፍሪካ ሀገራትን መበቀል ትፈልጋለች አሉ

Date:

የሩሲያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ፣ ኪዬቭ የአፍሪካ አገራት በዩክሬን ግጭት ዙሪያ በያዙት አቋም የተነሳ ልትብል እንደምትፈልግ ገልጸዋል፡፡

ዩክሬን የአሸባሪነት ባህሪዋን በድጋሚ አረጋግጣለች ሲሉ ማሪያ ዛካሮቫ መናገራቸውን የዘገበው ስፑትኒክ ነው፡፡

“የኪዬቭ አገዛዝ ታጣቂዎችን በማሠልጠንና የኔቶ ሀገራት ለዩክሬን የሚያቀርቡትን መሳሪያ በማስታጠቅ ጥቃቶች እንዲፈጽሙ እገዛ ያደርጋል፤ ይህ ሁሉ በአውሮፓ ኅብረት የሚሸፈን ነው” ሲሉ በጋዜጣዊ መግለጫ ወቅት አንስተዋል።

የኪዬቭ አገዛዝ ደጋፊዎች የአፍሪካን አህጉር ከሩሲያ ጋር ወደ ግጭት ለመሳብ የተቻላቸውን ሁሉ እያደረጉ ይመስላል ሲሉም ቃል አቀባይዋ ገልጸዋል።

“የኪዬቭ ባለሥልጣናት በዩክሬን ዙሪያ ባለው ሁኔታ በያዙት ተጨባጭ አቋም የተነሳ አፍሪካውያንን እየተበቀሉ እንደሆነ በግልጽ ይታያል” ብለዋል።

ሩሲያ በበኩሏ፤ ለአፍሪካ ሀገራት አስተማማኝ አጋር በመሆን፤ ያለፖለቲካዊ ጣልቃገብነትና ድርብ መስፈርት ለአኅጉሪቱ ሰላምና ደህንነት ቅድሚያ እንደምትሰጥ ዛካሮቫ ማስታወቃቸውን ስፑትኒክ ዘግቧል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ሕጻኑ በሀገሪቱ የመጀመሪያ በሆነ ቀዶ ሕክምና ተወለደ

የ28 ዓመቷ ወይዘሮ ሰናይት ታምራት ቀደም ሲል በነበረው እርግዝናዋ...

ግብፅ የኤርትራን ሉዓላዊነትና የግዛት አንድነት እንዲከበር ድጋፍ እንደምታደርግ ገለጸች

የግብፅ ፕሬዝዳንት አብድል ፈታህ አልሲሲ፤ የኤርትራን የግዛት አንድነትና ሉዓላዊነት...