አቶ አለማየሁ ፋንታ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል

Date:

በባህላዊ የሙዚቃ መሳሪያ ተጫዋጭነታቸው የሚታወቁት ሙዚቀኛው አለማየሁ ፋንታ ስራቸውን የጀመሩት ሃገር ፍቅር ቲያትር ቤት በመቀጠር ነው፤ እዚያም ለ10 ዓመታት ሰርተዋል፡፡

ለ40 ዓመታት ያህል በ ያሬድ የሙዚቃ ትምህርት ቤት በመምህርነት ሲያገለግሉ የቆዩት ሙዚቀኛው፤ በዕድሜአቸው መጨረሻ ጡረታ ከውጡ በኋላ በዚሁ ያሬድ ሙዚቃ ትምህርት ቤት ማገልገላቸውን የሙዚቀኛው የቅርብ ሰው ሆኑት ታዋቂው የበገና መምህር መጋቢ ብሉይ አለሙ አጋ ነግረውናል፡፡

ባህላዊዎቹን የኢትዮጵያ የሙዚቃ መሳሪያዎች በገናን በመደርደር፣ ክራርና መሰንቆን አሳምረው በመጫወት ይታወቁ እንደነበር ከመጋቢ ብሉይ አለሙ አጋ ሰምተናል፡፡

አንጋፋው ሙዚቀኛ አለማየሁ ፋንታ የቀለም ትምህርትን የተማሩ እንዲሁም የድቁና ትምህርትም የነበራቸው ነበሩ፡፡

ሙዚቀኛው ከ6 ወራት በፊት በድንገት ወድቀው እግራቸው በመሰበሩ በህክምና ሲረዱ ቆይተው በትናንትናው እለት መጋቢት 1 ቀን 2017 ዓ.ም ከዚህ አለም በሞት ተለይተዋል፡፡

ስርዓተ ቀብራቸው በነገው ዕለት ፒያሳ በሚገኘው በገነተ ፅጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ከቀኑ በ9 ሰዓት ይፈፀማል።

አንጋፋው ሙዚቀኛ አለማየሁ ፋንታ ባለ ትዳርና 6 ልጆች አባት ነበሩ፡፡

ቀዳሚ ጽሑፍ
ቀጣይ ጥሑፍ

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ኢትዮጵያ የ1 ቢሊዮን ዶላር የቦንድ ዕዳዋን ለማዋቀር ስታደርግ የነበረዉ ድርድር ያለ ስምምነት ተቋረጠ

የኢትዮጵያ መንግሥት በ2024 ዓ.ም. ዋናው ዕዳ የሚከፈልበት የአንድ ቢሊዮን...

የትግራይ ኃይል አባላት ሰልፍ ዛሬም በሌላ አቅጣጫ ቀጥለዋል

በመቐለና ዙሪያዋ የሚገኙ የትግራይ ኃይል አባላይ ትናንት ሰኞ ጥቅምት...

የምርመራ ኬዝ ስለሆነ ጥንቃቄ ያስፈልገዋል

ተማሪ ሊዛ ደሳለ የተባለች ወጣት ሰሞኑን በደሴ ከተማ “...

ስቲሊ አር.ኤም.አይ ላለፉት አራት ዓመታት የፕላቲኒየም ሸልማት ተሸላሚው

የ2017 በጀት ዓመት 7ኛው የታማኝ ግብር ከፋዮች ዕውቅና እና...