ቤት ገንቢዎች በርቱ ቀጥሉበት የሚባሉበት አዋርድ ሊካሄድ ነው።
ገንቢዎች በሰሩትና ባበረከቱት ልክ የሚመሰገኑበት የእውቅና አዋርድ ሊካሔድ መሆኑ ሰምተናል።
አዋርዱ አዳዲስ ወደ ዘርፉ የመጡ አልሚዎች ተነሳሽነት መጨመር አላማው እንደሆነ ነው የተገለጸው።
እንደዚሁም ቤትና የስራ ቦታ ፈላጊዎች ትክክለኛ አልሚዎችን የሚያዩበትና የሚለዩበት መሆኑ ተነግሯል።
በየአመቱ አልሚዎች የሚበረታቱበት የክብር ሽልማት ሆኖ ማየት ነውም ተብሏል።
የኢትዮጲያ የዘርፉ አልሚዎች በምስራቅ አፍሪካ ካሉ አልሚዎች በተሻለ ደረጃ ተቀምጠው ማየት የአዋርዱ ዋነኛ አላማ ነው ተብሏል።
ኢትዮ ሪል እስቴት የዕውቅና አዋርድ የተዘጋጀበት ዋነኛ ምክንያት፦
➢ ላይ ለመሳተፍ 20 ያህል አልሚዎች ከአርኪ ኤቨንት ኦርጋናይዘር ጋር የቅድመ ተሳትፎ ውል ተዋውለዋል፡፡
➢ ከተመዘገቡት የከተማችን ሪል እስቴቶች መካከል 100 በመቶ ያህሉ የዶክመንተሪ ቀረፃ ተደርጎ ተጠናቋል ተብሏል።
➢ የሪል እስቴት አልሚዎች እውቅና የሚያገኙባቸው የተሳትፎ ዘርፍ ቅፅ ተበትኗል በተቀመጠለት ጊዜ ይሰበሰባል፡፡
➢ የኢትዮ ሪል እስቴት የምዘና ቡድን አባላት የተሰበሰቡበትን ሰነዶች በመከፋፈል ምዘና ካካሄዱ በኃላ ውጤት ያስቀምጣሉ፡፡
➢ የተዘጋጀ የእውቅና ዘርፍ በዝግጅቱ እለት ይታወጃል፡፡
➢ በስሩት ልክ ባለሙት ልክ እውቅና ያገኛሉ፡፡
በኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ባለስልጣን፣ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የዘርፉ ምሁራን ተሳትፎ እንዲሁም በአርኪ ኤቨንት ኦርጋናይዘር አዘጋጅነት የተዘጋጀ መሆኑ ተነግሯል።
የሽልማት መርሀግብሩ ነሀሴ 25 ቀን 2017 ዓ.ም በስካይላይት ሆቴል ይካሄዳል ተብሏል።
