ኢንፊኒክስ ኢትዮጵያ እና ተግባረ-ዕድ አብሮ ለመስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራረሙ

Date:

በትራንስሽን ማኑፋክቸሪንግ ኃ.የተ.የግ.ማ ባለቤትነት የተያዘው ኢንፊኒክስ እና የአዲስ አበባ ተግባረ-ዕድ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ወጣቱን በቴክኖሎጂ ዘርፍ ለመደገፍ እና አብሮ ለመስራት የሚያስችላቸውን የመግባቢያ ስምምነት ዛሬ ጥቅምት 18/2018 አ.ም ተፈራርመዋል ።

የመግባቢያ ስምምነቱም የኢንፊኒክስኒ ክለብን በተግባረ ዕድ ፖሊ ቴክኒክ  ኮሌጅ ለማቋቋም የሚያስችለው ነው ተብሏል።

በዚህም ተማሪዎቹ በግል እና ሙያዊ እድገት ላይ ያተኮሩ ወርክሾፖች እና የማማከር ፕሮግራሞች ውስጥ እንዲሳተፉ እድል እንደሚሰጥ ተገልጿል ።

እንዲሁም መምህራን የቴክኖሎጂ ስልጠና እንደሚያገኙ ተጠቅሷል።

ስለ ስምምነቱ አስፈላጊነት የገለፁት የአዲስ አበባ ተግባረ እድ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዲን ዶ/ር ተሰፋዬ አድማሱ “ይህ የመግባቢያ ስምምነት ከጽሑፍ ሰነድ በላይ ነው ብለዋል።

የኮሌጁ ተማሪዎችም ከተግባራዊ ልምድ በተጨማሪ የስራ እድላቸውን እና በራስ መተማመናቸውን የሚያሳድጉበት መሆኑ ተጠቅሷል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የ12ኛ ክፍል መልቀቂያን ከ500 በላይ ላመጡ ተማሪዎች ማበረታቻና እውቅና ተሰጠ

በ2017 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ከ500 በላይ...

በኖኖ ጃዊ ቀበሌ የሚኖሩ 14 ኦርቶዶክሳውያን በአሰቃቂ ሁኔታ ተገደሉ

በአርሲ ሀገረ ስብከት ጉና ወረዳ በሚገኘ ኖኖ ጃዊ ቀበሌ...

ትራምፕ ከጃፓን ጠቅላይ ሚኒስትር ጋር በንግድ እና ወሳኝ ማዕድናት ላይ ንግግር አደረጉ

የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ማክሰኞ እለት የጃፓን የመጀመሪያዋ...

አንዳንድ የታችኛው ተፋሰስ ሀገራት በአባይ ወንዝ እኔ ብቻ ልጠቀም የሚለው አቋማቸው እንደከሸፈ ሊገነዘቡ ይገባል

ታላቁ ታላቁ የሕዳሴ ግድብ የቅኝ ግዛት አስተሳሰብን በመቀልበስ የተፋሰሱን...