ኤ.አይ.አይ.ቢ በኢትዮጵያ ያለውን አጋርነት በማጥበቅ ለመሠረተ ልማት ፕሮጀክቶች ድጋፍ ለማድረግ ተስማማ

Date:

የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ ከአለም ባንክና IMF ዓመታዊ ስብሰባ ጎን ለጎን ከእስያ መሠረተ ልማት ኢንቨስትመንት ባንክ (ኤ.አይ.አይ.ቢ) ምክትል ፕሬዚዳንት ሚስተር አጃይ ቡሻን ፓንዴይ ጋር መምከራቸው ተዘግቧል።

ሚኒስትሩ፣ የልማት አገሮችን ለመደገፍ ዝቅተኛ የወለድ ተመኖችን ማስፋት አስፈላጊ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል። በተጨማሪም ስለሚገነባው አዲስ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሜጋ ፕሮጀክት የዝግጅት ውይይት መጀመሩን ገልጸው፣ በተለይም በኢነርጂው ዘርፍ የ AIIB ድጋፍ እንዲሰጥ ጠይቀዋል።

ፓንዴይ በበኩላቸው የኢትዮጵያን የኢኮኖሚ ማሻሻያ እና ለመሠረተ ልማት ያለውን ቁርጠኝነት አድንቀዋል።

ሁለቱም ወገኖች ትብብራቸውን በማጠናከር፣ በተለይም በትራንስፖርት፣ ኢነርጂና ትስስር ላይ ለሚያተኩሩ የለውጥ አምጪ ፕሮጀክቶች የባንኩን ድጋፍ በፍጥነት በማሰባሰብ የገንዘብ ድጋፍ ለማድረግ ቃል ገብተዋል።

ቅዳሜገበያ

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የኢመማ 23ኛ ጠቅላላ ጉባኤ በአዲስ አበባ እና በአዳማ ከተሞች ተካሔደ

የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር 23ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ የመክፈቻው ሥነ_ሥርዓት...

ሐጅ ኡመር ኢድሪስ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

የቀድሞው የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ተቀዳሚ...

ረቂቅ መመሪያ ተዘጋጀ

ከባንኮች ከፍተኛ ድርሻ የሚገዙ አካላት የገንዘባቸውንምንጭ እንዲያሳውቁ የሚያስገድድ ረቂቅ...