የቤተ ክርስቲያኗ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባዔ ዓለም አቀፍ መደበኛ ስብሰባ መካሄድ ጀመረ

Date:

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ አጠቃላይ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባዔ 44ኛው ዓለም አቀፍ መደበኛ ስብሰባ መካሄድ ጀምሯል፡፡

በጉባኤው ላይ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስን ጨምሮ በመላው ዓለም የሚገኙ አህጉረ ስብከት ተወካዮች እየተሳተፉ ሲሆን ፓትርያርኩ በዚህ ወቅት ባስተላለፉት መልዕክት፤የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያንን በጥበብ በመምራት፣ ለመጭው ትውልድ ማሻገር እንደሚያስፈልግም ተናግረዋል፡፡

በጉባኤው ላይ በቤተ ክርስቲያንና ገዳማት ላይ የሚያጋጥሙ ችግሮች ቀርበው የመፍትሔ ሐሳቦች ይሰጥባቸዋል የተባለ ሲሆን፤ ቤተ ክርስቲያኗ ያከናወነቻቸው ተግባራት ቀርበው ውይይት እንደሚደረግባቸውም ተጠቁሟል፡፡

በየዓመቱ በጥቅምት ወር በሚካሔደው በዚህ ጉባኤ ለቤተክርስቲያን አገልግሎት የሚጠቅሙ፣ ለመንፈሳዊ አስተዳደሯም የሚበጁ መሠረታዊ ጉዳዮች ይቀርባሉ። በሚቀርቡት ሪፖርቶች ላይም ውይይትና የልምድ ልውውጥ ተደርጎ የላቀ ውጤት ያስመዘገቡ ይሸለማሉ፤ ዝቅተኛ አገልግሎት ይዘው የመጡ ደግሞ ከጉባኤው ልምድ ቀስመው አገልግሎታቸውን እንዲያሻሽሉ ይመከራሉ ተብሏል።

መደበኛ ስብሰባው ከዛሬ ጥቅምት 4 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ለአምስት ቀናት እንደሚቀጥል ታውቋል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ኢትዮጵያ የ1 ቢሊዮን ዶላር የቦንድ ዕዳዋን ለማዋቀር ስታደርግ የነበረዉ ድርድር ያለ ስምምነት ተቋረጠ

የኢትዮጵያ መንግሥት በ2024 ዓ.ም. ዋናው ዕዳ የሚከፈልበት የአንድ ቢሊዮን...

የትግራይ ኃይል አባላት ሰልፍ ዛሬም በሌላ አቅጣጫ ቀጥለዋል

በመቐለና ዙሪያዋ የሚገኙ የትግራይ ኃይል አባላይ ትናንት ሰኞ ጥቅምት...

የምርመራ ኬዝ ስለሆነ ጥንቃቄ ያስፈልገዋል

ተማሪ ሊዛ ደሳለ የተባለች ወጣት ሰሞኑን በደሴ ከተማ “...

ስቲሊ አር.ኤም.አይ ላለፉት አራት ዓመታት የፕላቲኒየም ሸልማት ተሸላሚው

የ2017 በጀት ዓመት 7ኛው የታማኝ ግብር ከፋዮች ዕውቅና እና...