የትግራይ ኃይል አባላት ሰልፈኞች ለአራተኛ ቀን የመኪና መንገድ ዘግተዋል

Date:

ጥቅምት 6/2018 ዓ.ም የትግራይ ምስራቃዊ ዞን ዋና ከተማ ወደ ሆነችው የዓዲግራት ከተማ የሚያስገቡና የሚያስወጡ ሶስት ዋና መንገዶች ተዘግተዋል።

ጥቅምት 5/2018 ዓ.ም ከዓድዋ ወደ ዓዲግራት ሲጓዝ ሴሮ በተባለ ቦታ መንገድ ተዘግቶበት ከሰዓት በኃላ ተከፎቶ ወደ ከተማዋ የተጓዘው የቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ አባል እንዳረጋገጠው ፤ ከዓዲግራት ወደ መቐለ ዓድዋና ዛላአንበሳ አቅጣጫ የሚያመሩ መንገዶች ተዘግተዋል።

ከጥቅምት 3/2018 ዓ.ም ወዲህ ከክልሉ ምስራቃዊ ፣ ደቡባዊ ዞኖች ወደ መቐለ የሚወስዱ መንገዶች በኣጉላዕና ፣ በመኾኒ ወደ እንዳስላሰ-ሽረ ከተማ የሚወስድ መንገድ በእንዳባጉና ከዓድዋ ወደ ዓዲግራት የሚወስድ በሴሮ ተዘግተው በዚያው ቀን በተለያዩ ሰዓቶች መከፈታቸው ይታወሳል።

የክልሉ ካቢኔ በመንግስት የኮሙኒኬሽን ቢሮ በኩል ጥቅምት 5/2018 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ፤ የሰራዊቱ አባላት ያነሱት የደመወዝ ጭማሪ  የጥቅማ ጥቅምና የመሬት ጥያቄ ለመመለስ የሚያስችል መመሪያ ማውጣቱን ትላንት አሳውቆ ነበር። ያም ቢሆን ግን ዛሬም መንገዶች ተዘግተዋል።

@tikvahethiopia

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በ7.2 በመቶ ያድጋል ተብሎ ይጠበቃል

ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (አይ ኤም ኤፍ) ለመጠናቀቅ ሁለት...

ሽልማቱ ለሜቄዶንያ የአረጋውያን እና የአእምሮ ህሙማን መርጃ ማህበር ማስታወሻ ይሁንልኝ

የ2025 የአፍሪካ ኢምፓክት አዋርድ ሽልማትን ለሜቄዶንያ የአረጋውያን እና የአእምሮ...

በአክሱም ዩንቨርስቲ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ በእሳት አደጋ በሚሊዮኖች የሚገመት ንብረት ወደመ

በአክሱም ዩኒቨርስቲ ጤና ሳይንስ ኮሌጅና አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል መንስኤው...