የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ከ59 ቢሊየን ብር በላይ እንደሚያስፈልገው ገለጸ

Date:

የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የተሻለ የትምህርት ተቋም ለመሆን በቀጣይ አምስት ዓመታት ውስጥ 59 ቢሊየን ብር እንደሚያስፈልገው የዩኒቨርሲቲው ተጠባባቂ ፕሬዝደንት ሳሙኤል ክፍሌ አስታወቁ።

ዩኒቨርሲቲው በአሁኑ ወቅት በዓመት ከአራት ቢሊየን ብር የመንግስት በጀት እንዲሁም ከአንድ ቢሊየን ብር የራሱ ገቢ ያገኛል።

ሆኖም ፕሬዝደንቱ ይህ በቂ እንዳልሆነና ዩኒቨርሲቲው የትምህርት ጥራቱን ለማሻሻል፣ ምርምሮችን ለማስፋፋትና ለተማሪዎች ምቹ የሆነ የትምህርት ከባቢ ለመፍጠር በዓመት ከ11 ቢሊየን ብር በላይ እንደሚያስፈልገው ተናግረዋል።

የገንዘብ እጥረት ዩኒቨርሲቲው እነዚህን ግቦች ለማሳካት በሚያደርገው ጥረት ላይ እንቅፋት እየሆነ መሆኑንም ፕሬዝደንት ሳሙኤል ክፍሌ ገልጸዋል።

ቅዳሜገበያ

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

BYD ከ115,000 በላይ የኤሌክትሪክ መኪናዎች ላይ ማሻሻያ እንደሚያስፈልጋቸው ገለጸ

የቻይናው ግዙፉ የኤሌትሪክ መኪኖች አምራች ቢ.ዋይ.ዲ በዲዛይንና በባትሪ ተከላ...

የትራምፕን ንግግር የህንድ መንግስት ስለ ጉዳዩ ምንም የማዉቀዉ ነገር የለም ብሏል

የሕንዱ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ የሩሲያን ነዳጅ ላለመግዛት መስማማታቸውን...

አቶ አህመድ ሽዴ ከእንግሊዝ የዓለም አቀፉ የልማት እና የአፍሪካ ጉዳዮች ሚኒስትር ጋር ተወያዩ

የገንዘብ ሚኒስትር አቶ አህመድ ሽዴ ከእንግሊዝ የአለም አቀፍ የልማት...