የኢመማ 23ኛ ጠቅላላ ጉባኤ በአዲስ አበባ እና በአዳማ ከተሞች ተካሔደ

Date:

የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር 23ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ የመክፈቻው ሥነ_ሥርዓት በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በአድዋ መታሰቢያ ሙዚያም ተካሂዷል፡፡ በዚህ ዕለት የተለያዩ እህት ማህበራት ተገኝተው የአጋርነት መልዕከት ያስተላለፉ ሲሆን ዶ/ር ዴኒስ ሲኞሎ የትምህርት ዓለም አቀፍ አፍሪካ አህጉር ዳይሬክተር ተገኝተው መልዕክት ከማስተላለፋቸውም በላይ ከጉባኤ አባላት ጋር በመሆን “Go public Fund Education” ዘመቻን መርተዋል፡፡

ጉባኤውን የትምህር ሚንስትር ተወካይ ዶ/ር ሰለሞን አብርሃም በንግግር ከፍተውታል፡፡እውቅናዎችም ለማህበሩና ለመምህራን የጎላ ድጋፍና አስተዋጽኦ ላደረጉ ድርጅቶችና ግለሰቦች ተሰጥቷል፡፡

የጠቅላይ ሚኒስቴር ጽ/ቤት፣ ፌደራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን፣ ኦሮሚያ ትምህርት ቢሮ፣ አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ፣ አሀዱ ሬድዮ ፣ ቬሎሲቲ ትራንስፖርት(ፕ.አል.ሲ)፣ ፐብሊክ ትራንስፖርት እንዲሁም በአፈጻጸማቸው የኦሮሚያ ክልል መምህራን ማህበር፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መምህራን ማህበር እና የማዕከላዊ ኢት/ክልል መምህራን ማህበር ዕውቅና ያገኙ ሲሆን በችግር ወቅት አባሎቻቸውን ላገለገሉ ለአማራ፣ ለትግራይና ለቤኒሻንጉል-ጉሙዝ ክልሎች እውቅና ተሰጥቷል፡፡

በግለሰብ ደረጃ አምባሳደር ዶ/ር ገነት ዘውዴ፣ አምባሳደር ዶ/ር ሽፈራው ሽጉጤ ፣ ከንቲባ አዳነች አቤቤ እና ማህበሩን ሲያገለግሉ ቆይተው በሌላ ለተተኩ የቀድሞ ክልል ማህበራት ፕሬዝደንቶች እንዲሁም ማህበሩን ለረጅም ዓመታት በትጋት ሲያገለግሉ ለነበሩት መ/ርት ደስታዬ ታደሰ የእውቅናው አካል ነበሩ፡፡ ከመክፈቻ ሥነስርዓት በኋላ የአፊሪካ ኮንቬንሽን ሴንተርን ጨምሮ በአዲስ አበባ በአራዳ፣ ለሚ ኩራና አቃቂ ቃልቲ ክፍለ ከተሞች የተለያዩ የልማት ሥራዎች ጉብኝት ተደርጓል፡፡

ጉባኤው ከጥቅምት 5-6/2018 ዓ/ም በአዳማ ከተማ በአባ ገዳ እኮኖሚ ዞን በሚገኘው የኦሮሚያ ክልል ትምህርት ቢሮ አዳራሽ በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ የመከረ ሲሆን በተለይ በትምህርት ጥራት ፣ መብትና ጥቅም፣ የመምህርነት ሙያ ተመራጭ አለመሆን ፣ ሰላም እና ሀገራዊ ጉዳዮች ፧ የተማሪዎች ወደ ት/ቤት መምጣት አለመቻል በተለይ በአማራ ክልል ያለው ሁኔታ ላይ ሲመክር ቆይቶ በሀገር ደረጃ ለቀጣይ ዓመታት ማህበሩን የሚመሩ ሥራ አስፈጻሚ እና የኦዲት ኮሚቴ አባላትን መርጧል፡፡

ተመራጮቹም
ዶ/ር ዮሐንስ በንቲ ፕሬዚዳንት ከኦሮሚያ፤
አቶ ሽመልስ አበበ ም/ፕሬዚዳንት ከአማራ፤
አቶ ጥላሁን ታረቀኝ ዋና ፀሐፊ ከትግራይ፤
ወ/ሮ መስታወት በላቸው ም/ዋና ፀሐፊና ስርዓተ ፆታ ኃላፊ ከኦሮሚያ ፤ እንስፔክተር ታረቀኝ ኃይሌ ትምህርት ስልጠናና ምርምር ኃላፊ ከደቡብ ኢትዮጵያ፤ ዶ/ር በፈቃዱ ዘለቀ የከፍተኛ ትምህርት ተወካይ ከኢትዮጵያ ዩኒቨርሲቲዎች (አዲስ አበባ ዩኒ.) ፤ ወ/ሮ ደብሪቱ ጌታቸው የኦዲት ኮሚቴ ሰብሳቢ ከድሬዳዋ፤ ወ/ሮ ገነት ከበደ የኦዲት ኮሚቴ አባል ከደቡብ ምዕ/ኢትዮጵያ፤ አቶ ታከለ ታደሰ ከሲዳማ ክልል የኦዲት ኮሚቴ አባል ሆነው ከተመረጡ በኋላ ባለ 12 ነጥብ የአቋም መግለጫ ወጥቶ ጉባኤው በተሳካ ሁኔታ ተጠናቋል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ሐጅ ኡመር ኢድሪስ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

የቀድሞው የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ተቀዳሚ...

ረቂቅ መመሪያ ተዘጋጀ

ከባንኮች ከፍተኛ ድርሻ የሚገዙ አካላት የገንዘባቸውንምንጭ እንዲያሳውቁ የሚያስገድድ ረቂቅ...