የኢትዮጵያ ካቶሊክ ጳጳሳት ጉባዔ በተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስ ሕልፈት የተሰማውን ሐዘን ገለጸ

Date:

የኢትዮጵያ ካቶሊክ ጳጳሳት ጉባዔ በተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስ ሕልፈት የተሰማውን ሐዘን ገልጿል፡፡

ጉባዔው ባስተላለፈው የሐዘን መግለጫ መልዕክት ÷ የኢትዮጵያ ካቶሊክ ቤተክርስቲያን በታላቁ አባት ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስ ሕልፈተ ሕይወት የተሰማትን ጥልቅ ሐዘን ትገልጻለች ብሏል፡፡

ተቀዳሚ ሙፍቲ የብዙዎች አባት፣ የሰላም እና የአንድነት ተምሳሌት ነበሩ፤ ሀገራችን ታላቅ አባትን አጥታለች ሲል ገልጿል፡፡

ከኢትዮጵያ ካቶሊክ ቤተክርስቲያን ጋር በተለይም በሀገራችን ሰላም እና እርቅን ለማውረድ በርካታ ሥራዎችን በጋራ እንደሰሩም አውስቷል፡፡

ጉባዔው ለቤተቦቻቸው፣ ለወዳጅ ዘመዶቻቸው፣ ለእስልምና እምነት ተከታዮች እና ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ መጽናናትን ተመኝቷል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የሙፍቲ ቀደምት ፎቶግራፍ

ይህ ፎቶግራፍ የተነሳው በ1965/1966 ሲሆን በፎቶው የሚታዩት የኢትዮጵያ እስልምና...

አገር ጥቁር ትልበስ!

ቃለ መጠይቅ የማድረግ እድል ሳገኝ ኢቲቪ ገብቼ ዓመትም አልሆነኝ።...

ታላቅ አረጋዊ ፣ የበሳል አእምሮ ባለቤት፣ አገርን የሚወዱ…

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት...

የተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስ አስከሬን ሽኝት እየተደረገለት ነው

የተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስ አስከሬን ከመኖሪያ ቤታቸው...