የእስራኤል ታጋቾች መለቀቅ

Date:



በሃማስና እስራኤል መካከል በተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት መሰረት የመጀመሪያው የታጋቾች የልውውጥ ሂደት መካሄድ ጀምሯል።

በዚህም ሀማስ ሰባት የእስራኤል ታጋቾችን ለቀይ መስቀል አስረክቧል። ቀይ መስቀልም የመጀመሪያ ታጋዮችን ለእስራኤል ወታደሮች ማስተላለፍ ተገልጿል ።

ታጋቾቹ በቀይ መስቀል እጅ መግባታቸውን የእስራኤል የቴሌቪዥን ጣቢያዎች ሲያስታውቁ፣ በሀገሪቱ በሚገኙ የህዝብ ማሳያዎች እና በቴል አቪቭ በሚካሄደው ዋና ዝግጅት ላይ የተሰበሰቡ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ እስራኤላውያን በታላቅ ደስታና ጩኸት ስሜታቸውን እየገለፁ ይገኛል ።

በተደረሰው ስምምነት መሠረት ሀማስ አጠቃላይ 20 በሕይወት ያሉ ታጋቾችን ለመልቀቅ ቃል ገብቷል:: በምላሹም እስራኤል በእስር ላይ የሚገኙ ከ1700 በላይ ፍልስጤማውያን እስረኞችን ትለቃለች ተብሎ ይጠበቃል።

ይህ የመጀመሪያው የታጋቾች ልውውጥ ለሁለት  ዓመት የዘለቀው አውዳሚ ጦርነትን ለማቆም በሚደረገው ጥረት ውስጥ ወሳኝ ምዕራፍ ተደርጎ ተቆጥሯል።

NBCEthiopia

ሆኖ_መገኘት

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የህዳሴ ግድቡ ውዝግብ በፖለቲካዊ ሳይሆን በቴክኒካዊ መንገድ መፈታት አለበት

በአሜሪካ ውጪ ጉዳይ መሥሪያ ቤት የአፍሪካ፣ እና የመካከለኛው ምስራቅ...

የ7 የጋራ መኖሪያ ቤቶች የኤሌክትሪክ መስመር ዝርጋታ አለመከናወኑ ተገለጸ

በአዲስ አበባ ቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን የሚተዳደሩ 7 የጋራ መኖሪያ...

የቀድሞው የኬንያ ጠቅላይ ሚኒስትር ራይላ ኦዲንጋ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

የቀድሞው የኬንያ ጠቅላይ ሚኒስትር ራይላ ኦዲንጋ በ80 ዓመታቸው ከዚህ...