የደራሲ ሕይወት ተፈራ የምንጊዜም ሶስት ምርጥ የሙዚቃ ምርጫ

Date:

“የከፊል ጊዜ ጸሐፊ ነኝ” የምትለው ሕይወት ተፈራ ከሀገር ከወጣች ከዘመናት በኋላ ወደ ኢትዮጵያ ተመልሳ ‘Tower In The Sky’ በሚል መጽሐፏ ከአንባቢ ጋር ተዋወቀች።

የኢሕአፓን ዘመን ከራሷ አንጻር የተረከችበት ይህ መጽሐፍ የእሷን አቻዎቿን የወጣትነት ዘመናት ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ ስለነበር ተወደደላት። ከዚያ በኋላም ሦስት ያህል መጻሕፍትን በእንግሊዘኛ እና በአማርኛ ማስነበብ ችላለች።

የሥነ ሰብ ጥናት (አንትሮፖሎጅ) የትምህርት መስኳ ሲሆን፣ በሐረር ተወልዳ፣ በአዲስ አበባ ተምራ ወደ ካናዳ አቅንታ ብዙ የሕይወት ልምድን ቀስማለች።

ሙዚቃ ማድመጥ እንደምትወድድ የምትናገረው ሕይወት ተፈራ፣ የኤፍ ኤም አዲስ 97.1 25ኛ ዓመትን ምክንያት በማድረግ የምንጊዜም ሦስት ምርጥ ዘፈኖቿን አሳውቃለች።

እነዚህም፦

የጥላሁን ገሠሠ “በምሽት ጨረቃ”
የሚካያ በኃይሉ “ሀገሬ”
የቴዎድሮስ ካሣሁን “ማ ዘንድ ይደር” ናቸው።

#FM97_1

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

BYD ከ115,000 በላይ የኤሌክትሪክ መኪናዎች ላይ ማሻሻያ እንደሚያስፈልጋቸው ገለጸ

የቻይናው ግዙፉ የኤሌትሪክ መኪኖች አምራች ቢ.ዋይ.ዲ በዲዛይንና በባትሪ ተከላ...

የትራምፕን ንግግር የህንድ መንግስት ስለ ጉዳዩ ምንም የማዉቀዉ ነገር የለም ብሏል

የሕንዱ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ የሩሲያን ነዳጅ ላለመግዛት መስማማታቸውን...

አቶ አህመድ ሽዴ ከእንግሊዝ የዓለም አቀፉ የልማት እና የአፍሪካ ጉዳዮች ሚኒስትር ጋር ተወያዩ

የገንዘብ ሚኒስትር አቶ አህመድ ሽዴ ከእንግሊዝ የአለም አቀፍ የልማት...