ፈንድቃ ባህል ማዕከል በቀጣይ የሚያስገነባውን ዘመናዊ የባህል ማዕከል ህንፃ ንድፍ ይፋ አድርጓል።
ፈንድቃ የባህል ማዕከል ስራ አስኪያጅ መላኩ በላይ በማህበራዊ ትስስር ገጽ “በካርሎ ራቲ አሶሺያቲ – የሚመራው በዓለም አቀፍ ታዋቂ የሆነው የኢጣሊያ የስነ ሕንፃ ተቋም – ለአዲሱ የፈንድቃ ህንፃ ንድፍ የመጀመሪያውን ምዕራፍ እንዳጠናቀቀ በማካፈሌ በጣም ደስተኛ ነኝ” ብሏል።
ፈንድቃ የባህል ማዕከል በጥቅምት 2017 ዓ.ም ከፈረሰ በኋላ በቦታው የራሱን ህንጻ እንዲሰራ ቦታው ለፈንድቃ መሰጠቱ ይታወሳል።
ከታህሳስ 2017 ዓ.ም ጀምሮ ፈንድቃ ከሀያት ሬጀንሲ ጋር በመተባበር ኮንሰርቶችንና እና አዝማሪ ፕሮግራሞችን እያቀረ ይገኛል።