ፕሬዝደንት ቭላድሚር ፑቲን ከሶሪያ ፕሬዝዳንት አህመድ አል ሻራ ጋር በሞስኮ ተወያዩ

Date:

የሩሲያው ፕሬዝደንት ቭላድሚር ፑቲን እና የሶሪያ አረብ ሪፐብሊክ ፕሬዝዳንት አህመድ አል ሻራ በክሬምሊን ውይይት አድርገዋል።

ሁለቱ ወገኖች በውይይታቸው በሀገራቱ መጻዒ የሁለትዮሽ ግንኙነት እና በሶሪያ የሚገኙ የሩሲያ ጦር ሠፈሮች ጉዳይ ላይ ትኩረት አድርገው መምከራቸው ተገልጿል፡፡

ፕሬዝደንት ቭላድሚር ፑቲን፤ በሁለቱ ሀገራት መካከል ለረዥም ዘመናት የቆየ ወዳጅነትና ግንኙነት እንዳለ አንስተው፤ በአልሻራ የሚመሩት ኃይሎች በሶሪያ ድል መቀዳጀታቸው ለሀገሪቱና ለህዝቡ ትልቅ ስኬት መሆኑን ገልፀዋል፡፡

ፕሬዝዳንት አህመድ አል ሻራ በበኩላቸው፤ አዲሱ የሶሪያ መንግሥት ከሩሲያ ጋር ያለውን ታሪካዊ ግንኙነት ማደስ እንደሚፈልግ ተናግረዋል፡፡

የሩሲያ ፕሬዝዳንት ቃል አቀባይ ዲሚትሪ ፔስኮቭ፤ በዛሬው ዕለት በሁለቱ መሪዎች መካከል የተደረገው ውይይት ለሩሲያ እና ሶሪያ ግንኙነት ወሳኝ ምዕራፍ መሆኑን መጥቀሳቸውን ስፑቲንክ ዘግቧል።

ebc

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

BYD ከ115,000 በላይ የኤሌክትሪክ መኪናዎች ላይ ማሻሻያ እንደሚያስፈልጋቸው ገለጸ

የቻይናው ግዙፉ የኤሌትሪክ መኪኖች አምራች ቢ.ዋይ.ዲ በዲዛይንና በባትሪ ተከላ...

የትራምፕን ንግግር የህንድ መንግስት ስለ ጉዳዩ ምንም የማዉቀዉ ነገር የለም ብሏል

የሕንዱ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ የሩሲያን ነዳጅ ላለመግዛት መስማማታቸውን...

አቶ አህመድ ሽዴ ከእንግሊዝ የዓለም አቀፉ የልማት እና የአፍሪካ ጉዳዮች ሚኒስትር ጋር ተወያዩ

የገንዘብ ሚኒስትር አቶ አህመድ ሽዴ ከእንግሊዝ የአለም አቀፍ የልማት...