ኤርትራ የኢትዮጵያን ክስ “ወታደራዊ ጠብ አጫሪነት” ነው አለች

Date:

ኢትዮጵያ ጦርነት ልትከፍትብኝ እየተዘጋጀት ነው ስትል የከሰሰቻት ኤርትራ፤ ክሱን “ወታደራዊ ጠብ አጫሪነት” ስትል ውድቅ አደረገች።

የኤርትራ የማስታወቂያ ሚኒስትር የማነ ገብረ መስቀል፤ «የቀድሞ ግዛትን ለማስመለስ ያለመ” ያሉትን ከፍተኛ የፕሮፓጋንዳ ዘመቻ፣ ወታደራዊ የጠብ አጫሪነት የታከለበት ነው ሲሉ ለፈረንሳይ ዜና አገልግሎት ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ለተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሐፊ አንቶንዮ ጉተሬቭ በላከው ደብዳቤ አስመራ ፣ ፅንፈኛ ካለው የህወሓት አንጃ ጋር ኢትዮጵያን ለመውጋት እየተዘጋጁ ነው ሲል ከሷል።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ጌድዮን ጢሞትዮስ የፈረሙበት ይህ ደብዳቤ፤ የፌደራል መንግሥት ወታደሮች ከአማጽያን ጋር በሚዋጉበት በአማራ ክልል «ሁለቱ አካላት የታጠቁ ቡድኖችን ይደግፋሉ፣ ያንቀሳቅሳሉ ይመራሉም” ሲልም ይወቅሳል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ጋዜጠኛ ተስፋዓለም ከዓለም የፕሬስ ነጻነት ጀግና ሽልማት ተሸላሚዎች አንዱ ሆኖ ተመረጠ 

ከ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” መስራቾች አንዱ የሆነው ተስፋለም ወልደየስ፤ ዓለም አቀፉ...

በአማራ ክልል በርካታ የደረጃ “ሀ” ግብር ከፋዮች ግብራቸውን አላሳወቁም

​አማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ በ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያዎቹ ሦስት...

ሁሉንም ኢትዮጵያዊ ምግቦች የያዘና ዓለም አቀፍ ደረጃውን በጠበቀ መዘርዝር (ካታሎግ) እየተዘጋጀ ነው

ሁሉንም ኢትዮጵያዊ ምግቦች የያዘ ዓለምአቀፍ ደረጃውን በጠበቀ መዘርዝር (ካታሎግ)...

በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ወደ ውጪ ሃገር ለሚላኩ ጭነቶች የስሪት አገር ማረጋገጫ ሰርተፊኬት ተሰጠ

የኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን በአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ ንግድ ስምምነት መሠረት...