አቶ አህመድ ሺዴ በG20 የጋራ ማዕቀፍ ምን አሉ

Date:



በማደግ ላይ ያሉ አገሮች የዕዳ ጫናን እንዲቋቋሙ ለመርዳት፣ በG20 የጋራ ማዕቀፍ ስር ሊተነበይ የሚችል እና ወቅታዊ የሆነ የዕዳ መልሶ ማዋቀር ዘዴዎች እንዲተገበሩ የገንዘብ ሚኒስትር ጠይቋል።

​ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ ይህንን ጥሪ ያቀረቡት በዋሽንግተን ዲ.ሲ. በተካሄደው የዓለም መንግስታት የሃያ አራት ቡድን (G-24) 114ኛው የሚኒስትሮች እና የገዢዎች ስብሰባ ላይ ሲሆን፣ ስብሰባው የ2025 የዓለም ባንክ እና የአይ.ኤም.ኤፍ ዓመታዊ ስብሰባዎች አካል ሆኖ ተካሂዷል።

​ሚኒስትሩ በንግግራቸው የዕዳ ማዋቀርን በተመለከተ መጠነኛ መሻሻሎች መኖራቸውን ቢገልጹም፣ በ G20 የጋራ ማዕቀፍ ስር ይበልጥ ሊተነበይ የሚችል እና ወቅታዊ የዕዳ ማዋቀር ዘዴ እንዲኖር የ G-24 መግለጫ ጥሪውን ማስተጋባታቸውን አረጋግጠዋል።

​በተጨማሪም አቶ አህመድ ሺዴ የቅናሽ ብድር፣ የታደሰ የብዙ ወገንተኝነት፣ የላቀ አብሮነት እና ለአደጋ ምላሽም ሆነ ለረጅም ጊዜ ልማት በማደግ ላይ ያሉ ኢኮኖሚዎችን የሚረዳ ዓለም አቀፍ ሥርዓት መኖር ወሳኝ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል።

CapitalNews

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

BYD ከ115,000 በላይ የኤሌክትሪክ መኪናዎች ላይ ማሻሻያ እንደሚያስፈልጋቸው ገለጸ

የቻይናው ግዙፉ የኤሌትሪክ መኪኖች አምራች ቢ.ዋይ.ዲ በዲዛይንና በባትሪ ተከላ...

የትራምፕን ንግግር የህንድ መንግስት ስለ ጉዳዩ ምንም የማዉቀዉ ነገር የለም ብሏል

የሕንዱ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ የሩሲያን ነዳጅ ላለመግዛት መስማማታቸውን...

አቶ አህመድ ሽዴ ከእንግሊዝ የዓለም አቀፉ የልማት እና የአፍሪካ ጉዳዮች ሚኒስትር ጋር ተወያዩ

የገንዘብ ሚኒስትር አቶ አህመድ ሽዴ ከእንግሊዝ የአለም አቀፍ የልማት...